ዳሩ ግን፦ እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ።
(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት1:15-16)
(ትንቢተ ሕዝቅኤል 36:20-23)
ወደ መጡባቸውም ወደ አሕዛብ በመጡ ጊዜ፥ ሰዎች እነርሱን፦ ከምድሩ የወጡ የእግዚአብሔር ሕዝብ እነዚህ ናቸው ሲሉአቸው ቅዱስ ስሜን አረከሱ። እኔ ግን የእስራኤል ቤት በመጡባቸው በአሕዛብ መካከል ስላረከሱት ስለ ቅዱስ ስሜ ስል ራራሁላቸው። ስለዚህ ለእስራኤል ቤት እንዲህ በል፦ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ በመጣችሁባቸው በአሕዛብ መካከል ስላረከሳችሁት ስለ ቅዱስ ስሜ ነው እንጂ ስለ እናንተ የምሠራ አይደለሁም። በአሕዛብም ዘንድ የረከሰውን፥ በመካከላቸው ያረከሳችሁትን ስሜን እቀድሰዋለሁ፤ በዓይናቸውም ዘንድ በተቀደስሁባችሁ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ አሕዛብ ያውቃሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፡፡
እግዚአብሄር እኔ በአህዛብ ፊት እናንተን ከነርሱ ውጡና የተለያችሁ ሁኑ እርኩሱንም ነገር አትንኩ ብያችሁ ነበር ነገር ግን እናንተ በመሃከላቸው ሆናችሁ ቅዱሱን ስሜን አረከሳችሁት: ስለዚህ እኔ እንደሎጥ እራራላችሁና እጃችሁን ይዤ አወጣችኋለሁ ለራሴ ለቅዱሱ ስሜ ስል እቀድሳችኋለሁ: ያኔ እናንተን ስቀድስ መልካም አድርጌ ስሠራችሁና በናንተ ውስጥ ስኖር አህዛብ እኔ እግዚአብሄር እንደሆንኩ ያውቃሉ እኔ እራሴ ስሜን አስከብራለሁ እናንተን እቀድሳለሁ እንደገናም በእናንተ እቀደሳለሁ ይላል ይህን የማደርገው ግን እናንተ ስለሰራችሁት ስለመልካም ስራችሁ ሳይሆን ስለራሴ ቅዱስ ስለሆነው ስሜ ነው ይላል ምክኒያቱም እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን እንድትሆኑ ስለምፈልግና እኔንም ማየት የምትችሉት በቅድስና ስትኖሩ ስለሆነ ነው፡፡
እንግዲህ መንፈሳዊ ቤት ሆናችሁ እንድትሰሩና እኔ እንድኖርባችሁ ይህን ከዚህ የሚቀጥለውን በመካከላችሁ አደርጋለሁ ይላል እግዚአብሄር፡፡
ከአሕዛብም መካከል አወጣችኋለሁ፥ ከየአገሩም ሁሉ እሰበስባችኋለሁ፥ ወደ ገዛ ምድራችሁም አመጣችኋለሁ። ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ፥ እናንተም ትጠራላችሁ፥ ከርኵሰታችሁም ሁሉ ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ። አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ፥ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ፥ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ። መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ፥ በትእዛዜም አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ። ለአባቶቻችሁም በሰጠኋት ምድር ትኖራላችሁ፤ ሕዝብም ትሆኑኛላችሁ እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ። (ትንቢተ ሕዝቅኤል 36:24-28) አሜን አሜን አሜን!!!
እባክዎን አንብበው ሲጨርሱ ላይክ የሚለውን ቢጫኑት ወደፊት የሚወጡ ጽሁፎችን በቀላሉ ማግኝት ይችላሉ በማንበብ ስለሚተባበሩኝም አመሰግንዎታለሁ
ካሱ ቦስተን
እባክዎን ካነበቡ በኋላ ላይክ የሚለውን ይጫኑ እንዲሁም መልእክቱን ለሌሎች ያካፍሉ አመሰግናለሁ