ቤተክርስቲያን ሆይ ንቂ ! ዛሬ ቤ/ክ የትኛውን ትመስል ይሆን ?

 ቤተ ክርስቲያን ከመሰረታትና ሙሉ ባለቤትነት ካለው ከክርስቶስ ተልዕኮ ተሰጥቷት በምድር ላይ ያለች የክርስቶስ አካል ነች፣ ቤተክርስትያን ላለፉት 2000 አመታት በብዙ ድልና በብዙ ውጣ ውረድ እንዲሁም በብዙ ችግሮች ውስጥ አልፋለች አሁንም እያለፈች ነው። ቤተክርስቲያን የሰው አይደለችም፣ የሐዋርያ፣ የፓስተርም፣ የነብይም፣ የወንጌላዊም፣ የአስተማሪም አይደለችም፤ ነገር ግን ሰው ሊያስተዳድራት ይችላል። 

     ቤተ ክርስቲያን የራሱ የእግዚአብሄር ሆና ሰዎችን ግን የተለያየ ጸጋና ስልጣንን በመስጠት ያስተዳድሯት ዘንድ በውስጥዋ አስቀምጧል። እዚህ ላይ ማወቅ ያለብን ሁላችንም ቤተክርስቲያን የእግዚአብሄር ናት ብለን ዝም እንድንል አይጠበቅብንም። በውስጧ ስንመላለስ በስርዓት እንወጣና እንገባ ዘንድ፤ እንዲሁም እግዚአብሄር በሰጠንም ጸጋና የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ እናገለግል ዘንድ፤ በቤቱ ውስጥ የሚያስቀምጣቸው ቤቱን እንዲመሩ ስልጣንን የሰጣቸው ሰዎች: የሰዎችን ጸጋ በማየት እንደስጦታቸው እንዲያገለግሉም ሊያደርጉ የሚገባቸው በመሪነት ቦታ ያሉ ሰዎች ናቸው ማለት ነው። እግዚአብሄር መጥቶ ቤቱን እንዲጠብቅ የምትመኙ ካላችሁ ተሞኝታችኋል። 

     መጽሐፍ ቅዱሳችን ቤተክርስቲያን ለሰራችው መልካምም ሆነ እንደ እግዚአብሔር ቃል ባልተመላለሰችበት ጉዳይ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ብድራትን እንደምትቀበል ያስተምራል፤ ቤተክርስቲያን በአገልግሎቷ፣ በአካሄዷ፣ በሃላፊነቷ፣ በተሰጣት የጸጋ ስጦታና በተሰጣት መንፈሳዊ ስልጣንና ኃይል ጉዳይ በኢየሱስ ክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት ትቆማለች፣ በዚህ የፍርድ ወንበር ፊት ትዳኛለች ትጠየቃለች፣ ከዛም እንደስራዋ ታገኛለች።

  ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና። ሮሜ 14፡10

እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን። ሮሜ 14፡12

     ጌታ ኢየሱስ ለዮሃንስ ራእይ 1፡11 ላይ እንዳዘዘው፦ “የምታየውን በመጽሐፍ ጽፈህ ወደ ኤፌሶንና ወደ ሰምርኔስ ወደ ጴርጋሞንም ወደ ትያጥሮንም ወደ ሰርዴስም ወደ ፊልድልፍያም ወደ ሎዶቅያም በእስያ ወዳሉት ወደ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ላክ።”  እንዳለው የራዕይ መጽሃፍ ያሳየናል። 

❄ 👉 እነዚህ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት በወቅቱ በትንሿ እስያ የሚገኙ አጥቢያዎች ነበሩ፤ እያንዳንዳቸው አብያተ ክርስቲያናት ጠንካራና ደካማ ጎኖች ነበራቸው፣ ኢየሱስም ለጠንካራ ጎናቸው ማበረታቻ፤ ለደካማ ጎኖቻቸው ደግሞ ምክር ሲሰጥና ሲገስጽ እንመለከታለን። ዛሬም በእነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የምናየው እኛ ያለንበትን የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተክርስቲያን ይሆናል። ዛሬም እንደዮሃንስ በመንፈስ የሚመራ ሰው ቢኖር ከጌታ ዘንድ በቦስተን ላለችው የኢትዮጵያ ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን እንዲህ ብለህ ጻፍና ላክ ቢባል ምን አይነት መልዕክት ይላክላት ይሆን ? እኔ ይህን ይህን ለማለት ባልችልም በተጻፈው በራዕይ መጽሃፍ ውስጥ ያለውን ካየን፤ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፏልና እንቀበለዋለን።  

 1 👉 የኤፌሶን ቤተክርስቲያን (ራእይ 2፡1-5)

    የኤፌሶን ቤ/ክ ስንመለከት የኤፌሶን ቤ/ክ ለክርስቶስ ስም ስትል ጸንታ የቆመች፣ ሐዋርያት ነን ባዮችን መርምራ ሐዋርያት አለመሆናቸውን የምታጋልጥ፣ ያልደከመች ቤ/ክ ነበረች፤ ግን የቀድሞ ፍቅሯን ትታለች፣ ለዚህም ውድቀቷ ከወዴት እንደ ወደቀች እንድታስብ ንስሐም እንድትገባ የቀደመውን ሥራዋን እንድታደርግ፤ አለዚያ ጌታ እንደሚመጣባት ንስሐም ባትገባ መቅረዝዋን ከስፍራው እንደሚወስድ ማስጠንቀቂያ ደርሷታል። ራእይ 2:1-5 የኤፌሶን ቤ/ክ በወቅቱ በትንሿ ኤስያ የምትገኝ ከተማ ነበረች፣ ኤፌሶን የንግድና ከሶስቱ የሮም ግዛቶች በጣም ዝነኛ ነበረች፣ ኤፌሶን ከተማ የአርጤምስ ቤተ ጣኦት መገኛም ነበረች (ሐዋ 19:21-41)

2 👉 ሰምርኔስ ቤተክርስቲያን (ራዕ 2፡9)

   የሰምርኔስ ከተማ ከኤፌሶን በስተምዕራብ በኩል በ25 ማይል ርቀት ትገኝ ነበር፤ በዚህ ከተማ ቤ/ክ ከሁለት ዋና ዋና ችግሮች ጋር ትጋፈጥ ነበር 1ኛ የአይሁድ ክርስትናን መቃወምና አይሁድ ያልሆኑ አምልኮተ ንጉስን መቀበላ ቸው ዋና ዋና ችግሮች ነበሩ።

3 👉 የፔርጋሞን ቤተክርስቲያን

   የፔርጋሞን ከተማ በ1000 ጫማ ከፍታ ባለው ከተማ ላይ የተመሰረተች ከተማ ነበረች፣ ከተማዋ የግሪክ ባህልና ስልጣኔ ማዕከል ነበረች፣ ከተማዋ የተለያዩ አይነት ጣኦቶች ነበሩባት፣ ፔርጋሞን በእባብ ራሱን በመሰለ ጣኦት የተሞላች ከተማ ነበረች፤ አማኞች በዚህ ከተማ ታላቅ ስደትና እምነታቸውን እንዲተው ግፊት ይደረግባቸው ነበር፣ በፔርጋሞን ይገኙ የነበሩ አማኞች በእምነታቸው ተመስክሮላቸዋል የተወቀሰችበትም ነገር አለ አንደኛ በስህተት ትምህርትና በስነምግባር ጉድለት።

4 👉 የትያጥሮን ቤተክርስቲያን (ራዕ 2፡20-22)

    ትያጥሮን ጥንት በሮማውያን የኤዥያ ግዛቶች ውስጥ አንዷ የነበረች ባለጠጋ ከተማ ነበረች። ይህች ከተማ በአሁኑ ወቅት ቱርክ ነች። ለዚህች ቤ/ክ ኢየሱስ ክርስቶስ ጠንካራ እና ደካማ ጎኗን በማንሳት ከደከመችበት ሁኔታ እንድትወጣ አምላካዊ ምክር ሲመክርና ሲገስጽ እናነባለን።

  የትያጥሮን ቤተክርስቲያን 5 ዋና ዋና ጠንካራ ጎኖች

1 > ፍቅር  

2 > እምነት  

3 > አገልግሎት 

4 > ትዕግሥት  

5 > ታላቅ ስራ

   በመቀጠል ኢየሱስ ክርስቶስ የዚህችን ቤ/ክ ሃጢአት/ውድቀት ይጠቅሳል።

    “ዳሩ ግን ነቢይ ነኝ የምትለውን ባሪያዎቼንም እንዲሴስኑና ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉ የምታስተም ረውንና የምታስተውን ያችን ሴት ኤልዛቤልን ስለምትተዋት የምነቅፍብህ ነገር አለኝ”

👉 በወቅቱ ሐሰተኛ ነብያቶች፣ ጣኦት የሚያመልኩ፣ ግልሙትና ውስጥ የገቡ ክርስቲያኖች በቤተክርስትያን ውስጥ ነበሩ።

5 👉 የሰርዴስ ቤተክርስቲያን (ራዕ 3፡1-2)

   የሰርዴስ ከተማ በወቅቱ ባለጠጋ የንግድ ከተማ እና በሙስና የምትታወቅ ከተማ ነበረች። 

የሰርዴስ ቤ/ክ ዋና ችግር 👇

ሥራህን በአምላኬ ፊት ፍጹም ሆኖ አላገኘሁትምና የነቃህ ሁን፥ ሊሞቱም ያላቸውን የቀሩትን ነገሮች አጽና። (ራእይ 3፡2)

6 👉 የፊልድልፊያ ቤተክርስቲያን(ራዕ 3:8-9) ⛪

    የፊልድልፊያ ከተማ በፔርጋሞን ህዝቦች የተመሰረተች ከተማ ነበረች ከተማዋ ከዘመናት በኋላ በመሬት መንቀጥቀጥ ልትጠፋ ችላለች፤ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዚህች ቤ/ክ ማበረታቻ እና ዋና ዋና ምክሮችን ይመክራታል።

7 👉 የሎዶቅያ ቤተክርስቲያን (ራዕ 3:16-17)

   የሎዶቅያ ከተማ በባንክ ስልጣኔና በጥጥ ንግድ እንዲሁም በህክምና ት/ት በተለይ በአይን ኩል ገናና ነበረች፣ የቤ/ክ ዋና ችግር የአቋም ችግር ነበር። ወይ ቀዝቃዛ አልሆነች ወይ ሙቅ/ትኩስ/ አልሆነችም ነበር። ሌላው የዚህች ቤ/ክ ድክመት ሃብታም ነኝ አንዳች አያስፈልገኝም ባይ መሆኗ ነው፣ ቤ/ክ ይህን ትበል እንጂ ጌታ ኢየሱስ እንዲህ ይላታል ። “ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ፥” (ራእይ 3፡17)

⛪ ከላይ በራዕይ መጽሐፍ ላይ ከተመለከትናቸው ሰባቱ አብያተክርስቲያናት እኛ ምን እንማርባቸዋለን ?? ⛪

  1. ➡️ፍቅር ላይ ያልተመሰረተ አገልግሎት፣ እምነት፣ ጽናት፣ ትጋት ከንቱ እንደሆነ እንማራለን።⛪
  2. ➡️ቤ/ክ ለሰራችው ድልም ሆነ ሽንፈት ከኢየሱስ የምትቀበለው ብድራት እንዳለ መማር እንችላለን። ⛪
  3. ➡️ቤ/ክ ከኢየሱስ ክርስቶስ በተሰጣት አላማ ላይ ብቻ ማተኮር እንዳለባት እንማራለን።⛪
  4. ➡️ቤ/ክ የእምነት ተጋድሎን በሚገባ መታገል እንዳለባት መማር እንችላለን ⛪
  5. ➡️ቤ/ክ በአስተምህሮ፣ በአካሄዷ፣ አቋም ያላት የጸናች መሆን እንዳለባት መማር እንችላለን። ⛪
  6. ➡️ቤ/ክ የትኛውንም አይነት የዲያብሎስን አሰራር መቃወም እንዳለባትና በምንም ሁኔታ እና እንቅስቃሴዎች መተባበር እንደሌለባት ⛪
  7. ➡️ቤ/ክ ከመንግሥት፣ ከቤተሰብ፣ ከግለሰብ የተለያዩ አይነት ተቃውሞ ሊደርስባት ይችላል ቢሆንም ግን ጌታ እንደተናገረን መፍራት እና ወደ ኋላ ማፈግፈግ እንደሌለብን እንማራለን። ⛪
  8. ➡️ቤ/ክ የሃሰት ትምህርቶችን በመቃወም ጤናማውን ትምህርት መከተል እንዳለባት ያስተምረናል። ⛪
  9. ➡️የተለያዩ አጋንንታዊ ልምምዶች ቤተክርስቲያን ልትቃወም ይገባታል ለምሳሌ በፔርጋሞን ቤ/ክ በወቅቱ ፈውስ ለመቀበል በተሳሳተ ትምህርት ራሱን አዳኝ ነኝ ብሎ ወደ ሚጠራው እባብ ይሄዱ ነበር። ⛪

⛪ ቤተክርስቲያን መጠንቀቅ ያለባት አደጋዎች ⛪

    ቤተክርስቲያን በዚህ ዘመን ከሰዱቃውያን፣ ከዘረኝነት እና ከኤልዛቤል መንፈስ ልትጠነቀቅና ልትርቅ እንዲሁም መንጋዎቿን ልታስተምር እና ልታነቃ ይገባታል። እስኪ እነዚህን ሰፋ አድርገን እንመልከታቸው፤ 

🚫 1. 👉 ከዘመኑ ሰዱቃውያን

    የሰዱቃውያን ታሪካዊ አመጣጥ

        ሰዱቃውያን በጌታችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የምድር የአገልግሎት ዘመን መኳንንቶች፣ ባለጠጋና የፖለቲካ መሪዎች ነበሩ። በወቅቱ እስራኤል በሮማዊያን ቅኝ ግዛት ውስጥ ነበረች። ሰዱቃውያን ሰርኧዲን በሚባል ምክር ቤት ውስጥ 70 መቀመጫ ነበራቸው፤ ሰዱቃውያን በእስራኤልና በሮማውያን መካከል ሰላምና መልካም ጉርብትና እንዲኖር የሚሰሩ በላይኛው እርከን (Upper Class) ላይ የሚገኙ ቡድኖች ነበሩ።

        ሰዱቃውያን የእስራኤል ሊቀ ጳጳሳት የበላይ መሪዎች በመሆን ህዝቡን በሃይማኖትም በፖለቲካም ያገለግሉ ነበር፤ ሰዱቃውያን አምስቱን በሙሴ የተጻፉትን መጽሐፍት ብቻ ነበር የሚቀበሉት ሌላውን የብሉይ ኪዳን ቅዱሳት መጻህፍት አይቀበሉም። ሰዱቃውያን የኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎት ቀንደኛ ተቃዋሚዎች ነበሩ፣ ሲሰብክ ስብከቱን ይተቻሉ፣ ተአምር ሲሰራ በአጋንንት ስም ነው አጋንንት የሚያወጣው ይላሉ፣ ሲፈውስ አይቀበሉም፣ የእነርሱ ስራ የመንፈስ ቅዱስን ስራ ዝም ብሎ መቃወም ነው፤ ነገር ግን ሃይል አልባ የሃይማኖት ስልጣናቸው፣ ተቃውሟቸው በኢየሱስ ላይ ምንም ለውጥ አላመጣም ነበር፣ በዚህም ዘመን የሰዱቃዊያን አይነት ማንነት ያላቸው አልጠፉም፣ አገልጋዮችን የማሳደድ ፕሮግራም እና ስትራቴጂ አውጥተው የሰይጣን ቀኝ እጅ የሆኑ በየመንደሩ በየህብረቱ እና በየቤተክርስቲያን ውስጥ የተሰገሰጉ እውነተኛ ወንድሞች የሚመስሉ ነገር ግን ያይደሉ የአምልኮ መልክ ያላቸው ኃይሉን የካዱ ብዙዎች ናቸው። እነዚህን ደግሞ መንጥሮ መለየትና ማውጣት ወደ እውነት እንዲደርሱ እውነትን ማስተማር እና መመለስ፤ ካልተመለሱ ደግሞ መለየት እንዲሁም መ-ለ-የት ያስፈልጋል ማለት ነው። 

    “የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ።” 2ጢሞ 3፡5

    የዘመኑ ሰዱቃውያን አነጣጥረው በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚቃወሙት 8ቱን ዋና ዋና ነገሮችን እንመልከት፦

    1. ➡️የነብያትን አገልግሎት ከቤተክርስትያን ውስጥ ማዳከም፤
    2. ➡️የፈውስና የተአምራት አገልግሎቶችን ማናናቅ፤
    3. ➡️አጋንንት የማውጣት ስጦታዎችን የውሸት ትእይንት አድርጎ መስበክ፣ ማውራት፣ ማናፈስ፤
    4. ➡️አምስቱን ቢሮዎች ከቤተክርስቲያን ውስጥ አስወግዶ ቤ/ክንን ባዶ ማድረግ፣ (ሐዋርያ፣ ነብይ፣ መጋቢ፣ አስተማሪ፣ ወንጌላዊ)፤
    5. ➡️ከመንፈስ ቅዱስ ሃሳብ ጋር የማይሄድ አስተሳሰብ እና አመራር በቤ/ክ ውስጥ መዘርጋት፤
    6. ➡️ሀይል አልባ ቲኦሎጂ ማስፋፋት፤
    7. ➡️ትንቢትን መናቅና ማናናቅ፤
    8. ➡️ሚዛናዊነት የጎደለው አመለካከትን ማስፋፋት ነው።

    🚫 2. 👉 ከዘረኝነት

    ዘረኝነት በአጥቢያ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲገባ የሚከሰቱ 12 ዋና ዋና አደጋዎች:-

    1. ➡️ቤ/ክ ሰማያዊ የሆነውን፣ ከሰማይ የተቀበለችውን አዲሱን ማንነት ትታ ስጋዊ በሆነው ምድራዊ ማንነት ብቻ በመመላለስ አዱሱን ፍጥረት ችላ ማለት ውስጥ ትገባለች። 
    2. ➡️ቤ/ክ ትልቁን የክርስቶስ ኢየሱስን ተልእኮ ጥላ/ዘንግታ በራሷ የስጋ ጉዳይ መጠመድ ትጀምራለች።
    3. ➡️አሮጌ ፍጥረት/ስጋዊነት በቤተክርስቲያን ውስጥ ይሰለጥናል።
    4. ➡️ቤ/ክ መንፈሳዊ ስልጣኗን እንዳትጠቀም አቅም ታጣለች።
    5. ➡️ቤ/ክ ቅዱስ ፍሬ ማፍራት ትታ የስጋ ስራዎች ውስጥ ትጠመዳለች።
    6. ➡️ቤ/ክ ሰዎች እንዳይድኑ መሰናከያ ልትሆን ትችላለች።
    7. ➡️የእግዚአብሔርን ቁጣ ትቀሰቅሳለች።
    8. ➡️ቤ/ክ ንጹህ አምልኮ ለእግዚአብሔር ማቅረብ ይሳናታል።
    9. ➡️ቤ/ክ መፈራረስ ውስጥ ትገባለች።
    10. ➡️በዘረኝነት ላይ ያተኮረ አደረጃጀት፣ አስተምህሮ፣ ስብከት፣ አገልግሎት እና ወዳጅነት ላይ ትወድቃለች።
    11.  ➡️በመጨረሻው ቀን ከስራ ሽልማት ትጎድላለች።
    12. ➡️ቤ/ክ የሃይልና የስልጣን አካል/ድርጅት ከመሆን ይልቅ ባዶ ትሆናለች።

    የራዕይን መልዕክት ለምታነብ በዚህ ዘመን ላለች የክርስቶስ አካል ለሆነች ለቤተክርስቲያን መልዕክቱ ተመሳሳይ ሲሆን መልካም ላደረገችበት እሰየው የሚያሰኝ ሲሆን መልካም ላላደረገችበት ላጠፋችበት እንደአጥቢያ ቤተክርስቲያን ግሳጼውን ተቀብላ ንስሃ መግባት እንዳለባት ማወቅ ይገባታል። ቤተክርስቲያን ሁሌም መንጋዎችዋን ይዛ በንስሃ ወደጌታ መቅረብ አለባት። አሁን እንደምናየው ግን የንስሃ ትምህርቱም ሆነ የንስሃ ጸሎቱ በቤተክርስቲያን የቀረበት ሁኔታ ይታያል።

    🚫 3. 👉 የኤልዛቤል መንፈስ እና አሰራሯ

       “በትያጥሮንም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፦ እንደ እሳት ነበልባል የሆኑ ዓይኖች ያሉት በእቶንም የነጠረ የጋለ ናስ የሚመስሉ እግሮች ያሉት የእግዚአብሔር ልጅ እንዲህ ይላል፦ ሥራህንና ፍቅርህን እምነትህንም አገልግሎትህንም ትዕግሥትህንም ከፊተኛውም ሥራህ ይልቅ የኋለኛው እንዲበዛ አውቃለሁ።

    ዳሩ ግን፦ ነቢይ ነኝ የምትለውን ባሪያዎቼንም እንዲሴስኑና ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉ የምታስተምረውንና የምታስተውን ያችን ሴት ኤልዛቤልን ስለምትተዋት የምነቅፍብህ ነገር አለኝ፤ ንስሐም እንድትገባ ጊዜ ሰጠኋት ከዝሙትዋም ንስሐ እንድትገባ አልወደደችም። እነሆ፥ በአልጋ ላይ እጥላታለሁ፥ ከእርስዋም ጋር የሚያመነዝሩትን ከሥራዋ ንስሐ ባይገቡ በታላቅ መከራ እጥላቸዋለሁ፤ ልጆችዋንም በሞት እገድላቸዋለሁ፤ አብያተ ክርስቲያናትም ሁሉ ኵላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደ ሆንሁ ያውቃሉ፥ ለእያንዳንዳችሁም እንደ ሥራችሁ እሰጣችኋለሁ።” (ራዕይ 2:18-23)  

      በመጽሃፍ ቅዱሳችን ሰይጣን በተለያየ መንገድ እንደሚገለጥ እና እንደሚመሰል የምናይባቸው ክፍሎች አሉ። ለምሳሌ በእንሰሳት ሲመሰል፦ በእባብ፣ በዘንዶ፣ በጊንጥ፣ በአንበሳ፣ እና በሌሎችም እንስሳት ይመሰላል። በሰው ሲመሰል ደግሞ በኤልዛቤል እንደሚመሰል ከላይ ያየነው የመጽሃፍ ቅዱስ ክፍላችን ያሳየናል። ኤልዛቤል ማነች የሚለውን እስኪ እንመልከት፦  

    👉 ኤልዛቤል ማነች ????

        ኤልዛቤል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ 23 ጊዜ የተጠቀሰች ሲሆን 22 ጊዜ በብሉይ ኪዳን 1 ጊዜ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ተጠቅሳለች። ኤልዛቤል ከጣዖት አምላኪ ቤተሰብ የተወለደች ጣኦት አምላኪ ነች፤ መጽሃፍ ቅዱስ ኤልዛቤልን ሐሰተኛ አስተማሪ ወይም አሳች አድርጎ ያሳየናል። የሲዶናዊያን ንጉስ የኤትበአል ልጅ ነበረች። አባቷ ኤትበአል የበአል አምልኮ ተከታይ ነበር። ኤልዛቤል የእስራኤላውያን ንጉሥ የሆነው የአክአብ ሚስት ነበረች። ኤልዛቤል እና አክአብ ወደ ንግስና ከመጡ በኋላ ለእስራኤላውያን የውድቀት እና የመንፈሳዊ ጨለምተኝነት፣ የሞራል ውድቀት ምክንያት ሆነዋል። ባልዋ በአልን እንዲያመልክ እና ክፋትንም እንዲያደርግ የገፋፋች፤ የበአል ነብያትን የምትቀልብ እና የእግዚአብሄርን ነብያት ግን ትገድል የነበረች እንዲሁም ኤልያስ የበአልን ነብያት ስላስገደለ በእርሱ ላይ ዛቻን የተናገረች እና ናቡቴንም ያስገደለች ነበረች። በመጨረሻም በኢዩ ትእዛዝ ከመስኮት ላይ የተፈጠፈጠች መሆኗን መጽሃፍ ቅዱስ ይነግረናል።

         ምንም እንኳን ኤልዛቤል በመስኮት ተፈጥፍጣ የተገደለች ቢሆንም፤ ዛሬ ላይ መንፈሷ በምድር ላይ ባሉ በቤተክርስቲያን ውስጥ በስፋት እየሰራችና ክርስቲያኖችን በተለይ አገልጋዮችን እያሳተች ትገኛለች። በምድር ላይ ያለ እያንዳንዱ በክርስቶስ ኢየሱስ አምኖ የዳነ ክርስቲያን ወደዘላለም ቤቱ እስኪሄድ ድረስ በምድር ላይ መንፈሳዊ ውጊያ ያካሂዳል። ይህ ውጊያ ከደም እና ከስጋ ጋር ሳይሆን መንፈሳዊ ውጊያ ነው። ስለሆነም እያንዳንዱ እንቅስቃሴ በመንፈስ የሚደረግ እንጂ በስሜት ተገፋፍቶ የሚደረግ ውጊያ አይደለም። እንደ አማኝ በምድር ላይ አሸናፊዎች፣ ብርቱዎች፣ ገዢዎች፣ አስፈሪዎች፣ ሆነን በክርስቶስ ተፈጥረናል። የተደረግነውን ማንነት በመጠቀም የዲያብሎስን ስራ ማፈራረስ የቤተክርስቲያን ድርሻ ነው። መንፈሳዊ ውጊያ የምናደርገው ሰይጣንን ለማሸነፍ ሳይሆን አሸናፊነታችንን ተጠቅመን በጨለማ ግዛት ያሉትን ሰዎች ለመታደግ ነው። ቤተክርስቲያን የአለም ብርሃን እና የምድር ጨው በመሆን የሰይጣንን ስራ በማፍረስ የእግዚአብሔርን መንግስት እንድታስፋፋ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሃይል፣ ክብር እና ስልጣን ተቀብላለች።

    የኤልዛቤል 16ቱ ዋና ዋና መገለጫዎቿ

    1. 👉 ጣኦት አምላኪ ሴት ነች
    2. 👉 ነፍሰ ገዳይ ሴት ነች
    3. 👉 የባልን ራስነት የማትቀበል ሴት ነች
    4. 👉 ልበ ደንዳና ሴት ነች
    5. 👉 ጋለሞታ ሴት ነች
    6. 👉 ባለቤቷን የምትነዳ ሴት ነች (1ነገ 20:25)።
    7. 👉 ክፉ መካሪ ነች
    8. 👉 ስነምግባር የሌላት ሴት ነች
    9. 👉 መተተኛ ሴት ነች
    10. 👉 ጨቋኝ ንግስት ነች
    11.  👉 ሐሰተኛ ነብይ ነች
    12. 👉 ሐሰተኛ አስተማሪ ነች
    13. 👉 ሴረኛ ሴት ነች
    14. 👉 ነብያትን የምታሳድድ ጠላት ነች
    15. 👉 ራስ ወዳድ ሴት ነች
    16. 👉 ፍትህ የምታጣምም ሴት ነች።

    “ዳሩ ግን። ነቢይ ነኝ የምትለውን ባሪያዎቼንም እንዲሴስኑና ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉ የምታስተምረውንና የምታስተውን ያችን ሴት ኤልዛቤልን ስለምትተዋት የምነቅፍብህ ነገር አለኝ፤ (ራእይ 2:20)

    ⛔️✴✴ የኤልዛቤል አላማዋ ✴✴⛔️

    1. የእግዚአብሔርን ህዝብ ለጣኦት እንዲገዙ እና እንዲሰግዱ ማድረግ።
    2. የእግዚአብሔር ህዝብ እንዲጎለትምቱ እና እንዲሴስኑ ማድረግ።

    3. የእግዚአብሄርን ህዝብ የሃሰትን ትምህርስት በማስተማር ከዓላማቸው ማሳት።

    👉 ኤልዛቤል ጋለሞታ ሴት ነች።


    ⛔️👉 የጋለሞታይቱ ሴት ባህሪዋ እና ምልክቶቿ ፦  ( ምሳሌ 7 )⛔️
    💢 ኤልዛቤል የተለየች ሆና ሰውን ሁሉ ለማጥመድ የምትችልበት የአለባበስ ዘዴ አላት፤  “እነሆ፤ ሴት ተገናኘችው የጋለሞታ ልብስ የለበሰች ነፍሳትን ለማጥመድ የተዘጋጀች።” (ምሳሌ 7፡10)

    💢 ኤልዛቤል ዘዋሪ እና አጥፊ ነች፤  “ሁከተኛና አባያ ናት፥ እግሮችዋም በቤትዋ አይቀመጡም።” (ምሳሌ 7:11)
    💢 ኤልዛቤል አ’ዳ’ኝ (የም’ታ’ድ’ን) ሴት ነች፤  “አንድ ጊዜ በጎዳና፥ አንድ ጊዜ በአደባባይ፥ በማዕዘኑም ሁሉ ታደባለች።” (ምሳሌ 7፡12)
    💢 ኤልዛቤል ከማንም ጋር አካላዊ ንኪኪ ትወዳለች፤ “ያዘችውም ሳመችውም፤ ፊትዋም ያለ እፍረት ሆኖ እንዲህ አለችው።” (ምሳሌ 7፡13)
    💢 ኤልዛቤል ማንንም አታፍርም፤ “ፊትዋም ያለ እፍረት ሆኖ እንዲህ አለችው።”(ምሳሌ 7፡13)
    💢 ኤልዛቤል እቤት አትቀመጥም እግሮችዋም በቤትዋ አይቀመጡም፤ መዞር ትወዳለች፤ “እግሮችዋም በቤትዋ አይቀመጡም።” (ምሳሌ 7፡11)
    💢 ኤልዛቤል ስለ ህይወት ደንታ ቢስ ነች፤  “እግሮችዋ ወደ ሞት ይወርዳሉ፥ አረማመድዋም ወደ ሲኦል ነው።” (ምሳሌ 5፡5)
    💢 ኤልዛቤል ጥፋቷን የማትቀበል አማፂ ነች፤  “እንዲሁ በልታ አፍዋን የምታብስ። አንዳች ክፉ ነገር አላደረግሁም የምትልም የአመንዝራ ሴት መንገድ ናት”  (ምሳሌ 30፡20)
    💢 ኤልዛቤል ሃይማኖታዊ ሆና መታየት ደስ ይላታል፤  “መሥዋዕትንና የደኅንነት ቍርባንን ማቅረብ ነበረብኝ፤ ዛሬ ስእለቴን ፈጸምሁ” (ምሳሌ 7፡14)
    💢 ኤልዛቤል ገዳይ ነች፤  “ወግታ የጣለቻቸው ብዙ ናቸውና፤ እርስዋም የገደለቻቸው እጅግ ብዙ ናቸው። (ምሳሌ 7፡26)
    💢 ኤልዛቤል ሙልጭልጭ እና ብልጣ ብልጥ ነች።
    💢ኤልዛቤል ውበቷን በመጠቀም ታጠምዳለች፤  “ውበትዋን በልብህ አትመኘው፤ ሽፋሽፍትዋም አያጥምድህ።” (ምሳሌ 6፡25)
    💢ኤልዛቤል በንግግር ታጠምዳለች፤ “ከጋለሞታ ሴት ከንፈር ማር ይንጠባጠባልና፥ አፍዋም ከቅቤ የለሰለሰ ነውና።” (ምሳሌ 5፡3)
    💢ኤልዛቤል ለወሲብ ግብዣ ታደርጋለች፤  “ና፥ እስኪነጋ ድረስ በፍቅር እንርካ፥ በተወደደ መተቃቀፍም ደስ ይበለን።” (ምሳሌ 7፡18)

     ⛔️ የኤልዛቤል አስተምህሮ ⛔️

    ቤተክርስቲያን ነቅታ ልትጋደል የሚገባት ሌላኛው የዘመኑ ተግዳሮት የኤልዛቤል አሰራርና አስተምህሮ ነው።

    አስተምህሮዎቿ ምን ይመስላሉ ?

    1. 👉 ድህረ ዘመናዊነት/postmodernism ይህ አስተሳሰብ እና ፍልስፍና በአንድ መንገድ ብቻ የሚገለጽ ሳይሆን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች የሚገለጽ ነው። ለምሳሌ በስነጽሑፍ፣በዘፈን፣በፊልም፣በፋሽን ፣በቴክኖሎጂ፣በትምህርት እና በማህ በራዊ ሚዲያዎች የሚቀነቀን ወይም የሚሰበክ የኤልዛቤል አስተ ምህሮ ነው። ድህረ ዘመናዊነት/postmodernism አለም አቀፍ እውነት የለም ብሎ የሚያምን ዘመናዊ አመለካከት ነው። እውነት የሚባለው ሰዎች የተስማሙበት እንጂ በራሱ የቆመ ነገር አይደለም ይላሉ።በዚህ አስተምህሮ እውነት ፍጹም ሳይሆን አንጻራዊ፤እውነት በቦታ፣ በሁኔታ በጊዜ ምክንያት የሚለዋወጥ ነው።

      ✳👉 ድህረ ዘመናዊነት/postmodernism/ በክርስትና ላይ ያመጣው ተጽእኖ

      ✔አለማዊነት

      ✔ቁሳዊነት

      ✔ሰውን ያማከለ አመለካከት መስበክ

      ✔ፍትወትን ማስፋፋት።

      ✔ሳይንስን የሁሉ ነገር ምንጭ ማድረግ

      ✔የፍቅር መቀዛቀዝ።

      ✔የእግዚአብሔርን ቃል ከዓለም ጋር ማቻቻል።

      💢ይሄ ሁሉ በዘመናችን ቤተክርስቲ ያን በግልጽ እያየን ያለ የኤልዛቤል አስተምህሮ ውጤት ነው። በአለም ላይ ያለች ቤተክርስቲያን የተለያዩ የሐሰት ትምህርት እየተገዳደራት ይገኛል።

      ⛔️ ሌሎች የኤልዛቤል ትምህርቶች ⛔️

      2. 👉አምላክ የለሽነት atheism፦ ይህ አስተምህሮ ሰው ሊያምን የሚገባው የሚታየውን እና የሚዳሰሰውን ብቻ ነው ብሎ ያስተምራል።

      3. 👉 ዳርዊኒዝም/ Darwinism /ኢቮሊሽነሪ ቲዎሪ) ፦ ይህ አስተምህሮ እግዚአብሔር መኖሩን ይክዳል፣ እውነት በሳይንስ መረጋገጥ አለበት ይላል። አምላክ የለም፣ ሰው ከእንስሳ የተገኘ እንስሳ ነው ይላል ።

      4. 👉ናቹራሊዝም / naturalism ፦ ይህ የኤልዛቤል አስተምህሮ የሰው ልጅ ሙሉ በሙሉ ትኩረቱን በምድር ላይ ማድረግ አለበት ይላል ።

      5. 👉 ማቴሪያሊዝም/ materialism ፦ ይህ አስተምህሮ ማንኛውም እውነት መረጋገጥ ያለበት ለፊዚክስ ቅድሚያ በመስጠት፣ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ነው ብሎ ያስተምራል። 

      ⛔️✴ማጠቃለያ✴⛔️

             ወንድሞቼ እነዚህ ከላይ የተመለከትናቸው በሙሉ የኤልዛቤል መገለጫዎችና ባህሪዋን እንዲሁም ምልክቷን እና አስተምህሮዋን ስንመለከት፤ ዛሬ በምድር ላይ ያለች ቤተክርስቲያን አቅሟን ያጣችበትና የደከመችበት፤ ለምድር ጨው መሆን ያቃታት፤ ለዓለም ብርሃን መስጠት የማትችል ደካማ የሆነችበት፤ ወደዓለም ልትሄድና ወንጌልን ለማያምኑት ለመስበክ አቅምን ያጣችበት፤ ዓለም እራሷ ከነስርዓቷ እና ከነኮተቷ ቤተክርስቲያን ዘልቃ መድረክ የያዘችበት እና የእውነትን ወንጌልን አሽቀንጥራ በመጣል፤ ወንጌሉን አንግባ ሃሰትን የምትናገር ሆናለች። ስለዚህ ወገኖቼ የኤልዛቤልን መንፈስ ከቤተክርስቲያን መድረክ ላይ አንስተን በመስኮት አሽቀንጥረን ልንፈጠፍጣት ይገባል እላለሁ።  

          በምድር ላይ ያለ እያንዳንዱ በክርስቶስ ኢየሱስ አምኖ የዳነ ክርስቲያን ወደ ሰማይ እስከሚሄድ ድረስ በምድር ላይ መንፈሳዊ ውጊያ ያካሂዳል።ይህ ውጊያ ከደም እና ከስጋ ጋር ሳይሆን መንፈሳዊ ነው። ስለሆነም እያንዳንዱ እንቅስቃሴ በመንፈስ የሚደረግ እንጂ በስሜት ተገፋፍቶ የሚደረግ ውጊያ አይደለም። እንደ አማኝ በምድር ላይ አሸናፊዎች ፣ ብርቱዎች፣ገዢዎች ፣አስፈሪዎች፣ ሆነን በክርስቶስ ተፈጥረናል። የተደረግነውን ማንነት በመጠቀም የዲያብሎስን ስራ ማፈራረስ የቤተክርስቲያን ድርሻ ነው። መንፈሳዊ ውጊያ የምናደርገው ሰይጣንን ለማሸነፍ ሳይሆን አሸናፊነታችንን ለማረጋገጥ ነው።

      ተጠናቀቀ !

      የእግዚአብሔር ድል ከእናንተ ጋር ይሁን !

      Kassu Boston

      የኤልያሴብና የጦቢያ ወዳጅነት ለመንፈሳዊ ኪሳራነት !

      በነህምያ ዘመን እንዲህ ሆነ፡፡ ነህምያ የኢየሩሳሌምን መፍረስና የበሮችዋን መቃጠል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ አለቀሰም፡፡ ከዚያም ከንጉሡ ፈቃድ አግኝቶ ኢየሩሳሌምን ሊሰራ በመጣ ጊዜ ሶስት ጠላቶች ተነሱበት፡፡ “ሐሮናዊውም ሰንበላጥ ባሪያውም አሞናዊው ጦቢያ ዓረባዊውም ጌሳም በሰሙ ጊዜ በንቀት ሳቁብን፡፡ ቀላል አድርገውንም ይህ የምታደርጉት ነገር ምንድን ነው? በውኑ በንጉሡ ላይ ትሸፍቱ ዘንድ ትወዳላችሁን? አሉን፡፡” ይላል (ነህ.2፥19) ከዚህም ሌላ በብዙ ማስፈራራትና ዛቻ፣ በደብዳቤም በሰውም ኢየሩሳሌም እንዳትሰራ የነህምያን ልብ ለመስበር ሞክረዋል፡፡ ነህምያ ግን የአምላኩ እጅ ከርሱ ጋር ነበረችና ሥራውን ጨረሰ

          ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ ግን የኢየሩሳሌምን መሰራት ሲቃወም የነበረው ጦቢያ መኖሪያ ፍለጋ ወደ መቅደሱ አዘገመ። ኤልያሴብ ከሚባለው ካህን ጋር በመወዳጀትም በእግዚአብሔር ቤት ጓዳ ለመቀመጥ ቻለ፡፡ ነህምያ ስለዚህ ነገር ሲናገር እንዲህ ይላል“ከዚህም አስቀድሞ በአምላካችን ቤት ጓዳዎች ላይ ተሹሞ የነበረው ካህኑ ኤልያሴብ ከጦቢያ ጋር ተወዳጅቶ ለሌዋውያንና ለመዘምራን ….. እንደ ህጉ የተሰጣቸውን ለካህናቱም የሆነውን የማንሳት ቁርባን አስቀድሞ ያስቀመጡበትን  ታላቁን ጓዳ አዘጋጅቶለት ነበር፡፡» (ነህ.13፥4-6) ይህ መንፈሳውያን ለሆኑ ሁሉ ታላቅ መልእክት አለው፡- የኢየሩሳሌምን መታነፅና መታደስ በፅኑ ሲቃወም የነበረው ተቃዋሚ ጠላት ጦቢያ ከእግዚአብሔር ቤት ውስጥ  ታላቁን ጓዳ ሲያገኝና በዚያ ሲቀመጥ ለነህምያና ዛሬም የነህምያ መንፈስ ለሆነላቸው እንዴት የሚያሳዝንና የሚያበሳጭ ነው ! ያውም የተሰጠው ታላቁ ጓዳ እንደህጉ ለሌዋውያን ለመዘምራን ለበረኞች ለካህናት በአጠቃላይ ለመቅደሱና ለታላቁ ንጉሥ ለእግዚአብሔር አገልጋዮች የተዘጋጀው መብል የሚቀመጥበት የከበረው ቦታ ነበር፡፡ መብል በሚቀመጥበት ቦታ ውስጥ የእግዚአብሔር ህዝብ ጠላት ጦቢያ ተቀምጦ ነበር፡፡ ካህኑ ኤልያሴብ ለጦቢያ ይህንን የእግዚአብሄርን ጓዳ፤ የከበረውን ስፍራ ሊሰጠው አስቀድሞ ስፍራን ጠርጎለት(አመቻችቶለት) ነበር። ኤልያሴብ ያደረገው ክፉ ስራ ነበር፤ ለምን ? የእግዚአብሄርን ህዝብ ሊያስጨንቁ፤ የእግዚአብሄር ህዝብ አምላኩን እንዳያመልክ ኤልያሴብና ጦቢያ ተወዳጅተው ነበር ይለናል። አሁንም እኔ እና አንተ አንቺ በእግዚአብሄር ቤት ክፉ የሆነን ስራ ለመስራት የተወዳጁትን ካህኑን ኤልያሴብ እና ጦቢያን፤ ከክፉ ስራችሁ ተመለሱ ልንላቸው ይገባል።

         ዛሬም በዚህ ቃል ራሳችንን እና መቅደሳችንን ማለትም እግዚአብሄርን ማምለኪያና ህብረት ማድረጊያ ስፍራዎቻችንን እንዲሁም መንፈሳዊ ጓዳችንን እንፈትሽ፡፡ ከካህኑ ወይም ከሐሰተኛ አገልጋዮች ጋር ተወዳጅቶ የእውነት ዓምድና መሰረት በሆነው በእግዚአብሔር ቤት ጓዳ ውስጥ የተቀመጠውን የዘመኑን ጦቢያ ሃሰተኛና አስመሳዩን እንንቃበት፡፡ ይህም የዘረኝነት እና የግለኝነት ባህሪ (ቤተክርስቲያንን እንደግል ንብረት ማየት) የመጣላት የመለያየትና የመከፋፈል ምክንያት የሆነው አሮጌው ሰው(ጦቢያ) ነው። ባለንበትም በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ በተለይ አሁንም ጦቢያ “አሮጌው ሰው” ገዝፎ የሚታየው በታላቁ የአገልጋዮች የመዘምራን የሌዋውያን ጓዳ ነውና ነህምያዎች ሆይ ይህንን ጓዳ ለማፅዳትና ለእግዚአብሔር ለመቀደስ “ለመለየት” እንትጋ። 

         ነህምያ ያደረገውን ተመልከቱ “ኤልያሴብም በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ ለጦቢያ ጓዳውን በማዘጋጀት ያደረገውን ክፉ ነገር አስተዋልሁ፡፡ እጅግም አስከፋኝ፡፡ የጦቢያንም የቤቱን እቃ ሁሉ ከጓዳ ወደ ውጭ ጣልሁ፡፡ ጓዳዎቹንም እንዲያነፁ አዘዝሁ፡፡ የእግዚአብሔርንም ቤት እቃዎች፣ የእህሉንም ቁርባን፣ እጣኑንም መልሼ በዚያ አገባሁ” (ነህ.13፥7-9) ይህ መልእክት ለኛም በዚህ ዘመን ላለን የወንጌል መልእክተኞች የተሰጠ የአደራ መልእክት ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቤት ጓዳዎች ውስጥ ከኤልያሴብ ጋር ተወዳጅቶ የእግዚአብሄርን ህዝብ የሚያስጨንቅ፤ ለህዝቡ ስቃይና ሃዘን እንዲሁም ጭንቀት ምንም አይነት ሃዘኔታ እና ርህራሄ የሌለውን ጨካኙን ጦቢያን ከኤልያሴብ ጋር ልናስወግደውና ልናፀዳ ይገባል፡፡ (ሮሜ.12፥1) ከጦቢያ፣ ከአሮጌው ሰው፣ ከስጋዊ ማንነት የፀዳ፣ የእውነት ዓምድና መሰረት የሆነውንም እውነተኛ የእግዚአብሔር መቅደስ ማግኘት ያስፈልገናል፡፡ ጦቢያ በተቀመጠበት ጓዳ የጠራና የሰባ የመንፈስ መብል (የሚያሳድግ የእግዚአብሄር ቃል) ስለማይገኝ ምዕመናን እንደሚገባ ማደግ አይችሉምና፡፡ 

          መንፈሳዊ ቤትን ለመስራት በመጀሪያ ጓዳን ማጽዳት አስፈላጊ መሆኑን ልንገነዘብ ያስፈልጋል ፡፡ ጓዳን ማጽዳት ስል ያለ እግዚአብሄር ጸጋ የሚያገለግሉ የሚያስተምሩ የሚሰብኩ የሚዘምሩ እረኛ፣ ነብያት፣ ሃዋርያት እና ዘማሪ የሆኑ እነዚህን ለይተን ማጽዳትና ጸጋው ያላቸውን መተካት ያስፈልጋል ባይ ነኝ። ቤቱ አዲስ ሲሆን ልንረሳው የማይገባን ነገር ከአሮጌ ቤት አሮጌ እቃ ለቤቱ እንደማይመጥነው ለአዲሱ መንፈሳዊ ቤትም በአዲስ ቅባት የተቀቡ ለቤቱ የሚመጥኑ የመገልገያ እቃዎች ያስፈልጋሉና፤ ነህምያዎች ነቅተን እንድንለይና ቤቱን እንድናሳምረው ያስፈልጋል።

            ሌላው ደግሞ ዛሬ ጦቢያ ሆኖ በቤተክርስቲያን የተቀመጠ አላፈናፍን ያለና የእግዚአብሄርን መንፈስ ያዳፈነ፤ በጥንቱ ቤታችን የነበረ ዓይነት የበዓል (የዓመቱ ገብርኤል፣ ሚካኤል፣ ማርያም ወዘተ ) አከባበር እኛም ቤት ( የእናቶች የአባቶች የወንድሞች የእህቶች የፓስተሮች ቀን) ብዛት ይሆን ? የእግዚአብሄር ህዝብ ሆይ ዓይናችንን፣ አስተሳሰባችንን እና ልባችንን ከኢየሱስ ላይ እንድናነሳ የሚያደርጉንን ኤልያሴብን እና ጦቢያን ነቅተንባቸው ሃሳባቸውን ለይተን እንድንመታው ይገባናል፡፡

      ተባረኩልኝ፡፡

      ካሱ ቦስተን 

          ይህንን ጽሁፍ ወደውት ከሆነ ላይክ በማድረግ እንዲሁም ድህረ ገጹን ሰብስክራይብ ቢያደርጉ ሌሎች ጽሁፎች ሲለቀቁ ወዲያው እንዲደርስዎት ይሆናል። ለሌሎች በማካፈልም የድርሻዎትን ይወጡ።

      እንዲሁም ከታች ባሉት ሌሎች ዌብሳይቶች ላይ ያገኙኛል ሊንኩን በመጫን ይፈልጉኝ አመሰግናለሁ።

      linkedin.com/in/kassuboston

      https://www.facebook.com/kasselsa97

      https://thelastbelldotcom.wordpress.com

      https://www.instagram.com/kasselsa97

      https://www.youtube.com/channel/UCXQeAJgDLecjaAb_7ZjJmoA

      Should Christians celebrate Christmas ?

      Christmas As A Holiday

      When you see the topic, you are asking those questions, Did I have to? why ? Is it once a year ? for those answers let us read the next…

      Christmas as a traditional holiday dates back as far as A.D 273. Two pagan holidays were celebrated on that day to honor the sun, so this holiday might have started then to counter these festivals. Some people still feel uncomfortable because of this, but many will agree that the gospel does not just transcend culture; it also transforms it. A theologian once said: “We hold this day holy, not like the pagans because of the birth of the sun, but because of him who made it.” Meanwhile, it is agreed that by the Western Church that March is the annunciation or immaculate conception of Jesus in Mary’s womb.
      Evergreen trees are used to symbolize eternal life; Candles to symbolize Christ as the light of the world; Holly stands for the thorns in the crown; red for the blood and death; and gifts to remind us of the gifts given to Jesus as a baby and how He is God’s saving gift to the world.

      Like every other baby, He was birthed in groanings, blood, and cries.
      In a manger, his audience was mainly lambs.
      But heaven’s light shone, and we heard the angels sing:
      Hosanna! Blessed be the name of our King!”

      Centuries later, and the birth of Jesus the Anointed is still a memory we can’t do away with. What happened nine months after the word of the Lord came unto Mary in that day is of eternal relevance to the world and all of humanity.
      It is celebrated every the 25th of December all over the world, but why? Not just why December, but also why celebrate it at all? Is Christmas beyond a dogmatic celebration?

      Christmas Beyond the Holiday

      No matter our reasons for celebrating Christ’s birth, what should be the most important is that it is a remembrance of Christ’s incarnation. We can gather to eat chickens, celebrate with (extended) families, do charity, have church meetings, but we must always remember that the reason for the season is that Christ came as was prophesied.
      People go about these days ignoring that the Lord will one day come to take the Saints with him to eternity; the argument goes around the fact that years have gone by, and if there truly is a God in heaven, he is slow. Death is agreed to be the end, but man must remember that the coming Jesus as man amidst men is the fulfillment of thousands of years of promise.
      When Adam and Eve ate of the fruit of the knowledge of good and evil in the garden of Eden, God made a promise to the devil. He said:
      “I will put enmity between you and the woman and between your offspring and her seed.
      He will crush your head, and you shall bruise his heel.”
      (Genesis 3)
      Many think this refers to the present discord between man and snakes, but it is not so. Firstly, it is not everywhere snakes are killed or that snakes kill men. Secondly, the serpent was only a representation of the devil as seen by Moses in a vision.
      The enmity God meant was that he would come to put an end to the union man now had with the devil because he believed the instruction of the devil over that of God. With time, it became clearer through further prophecies that God will come as a man, the kingdom shall be on his shoulders, and he will save his people from their sins. His people do not mean Israel alone, but even Gentiles shall come to the knowledge of his rising.
      The number one essence of Christ’s incarnation to us then is that we serve a God who is not slack according to his promises as some men think, but he is long-suffering and not willing that any should perish, but that all should come to repentance. (2Peter 3:9) Hallelujah! Christ is coming back, and the fulfillment of the prophecies of incarnation reminds us of this.
      Furthermore, we are assured that whatever God promises us shall be fulfilled. He is not a man that should lie, neither a son of man that he should repent. If he says, he will do it. So often, believers give up on God because of a delayed promise, victory, or blessing, but the precedence of Christ’s incarnation in the Holy Bible teaches us that we serve a God who can do what he has promised. He is the kind of God that promised Abraham a child and fulfilled it in his old age; he is the God who promised Joseph the throne and still kept his word despite the attack of the devil through man.

      One more lesson from God’s prophecy of Christ’s incarnation (Christmas) is how he promised that the seed is Him. Christ was not born of the will of man. In the same way, God said, “Let there be Light,” and there was light. He also said “a child shall be born of you” to Mary, and it was so. Of course, it is a miracle that a child was birthed without the mating of a man and woman, but this was also playing out God’s prophecies. Shall we then not celebrate such a miraculous birth of a miraculous being?
      Finally, the question to ask is, “why only the 25th of December?” Of course, the kind of celebration that occurs on the 25th of December can happen only once a year, or at the most twice. We cannot travel down-home, kill animals, decorate houses, and have large feasts every time.

      However, the truth is Christ’s incarnation has an eternal relevance to us, so our celebration of it should be eternal. In other words, the birth of baby Jesus should be celebrated by everyone who has enjoyed the salvation He brought, every day. Not just every day, but an hour, minute, and second. This definitely cannot be a festival, but in our hearts, we should always sanctify our thoughts in reverence of what He has made available. The communication that proceeds out of our mouths should show that, indeed, the savior is perfect; his sacrifice is complete, and those who receive him shall never perish.

      *ref: The Body of Believers in Christ

      Christmas is beyond a holiday; it is a way of life.

      Amen ! Hallelujah !

      If you liked this article, please like it and subscribe to the website so that you will receive other articles as soon as they are published. Also, do your part by sharing it with others. You can also find me on the websites below by clicking on the link and searching for me.

      kassuboston

      Thank you.

      https://www.linkedin.com/in/kassuboston

      www.youtube.com/@kassuboston

      https://www.tiktok.com/@kassuboston

      https://www.instagram.com/kasselsa

      https://www.facebook.com/kasselsa

      https://thelastbelldotcom.wordpress.com

      የእግዚአብሄር መንግስት ምንድን ናት ?

      የማቴዎስ ወንጌል 6፡33 ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።

      “የእግዚአብሔር መንግሥት ምንድን ነው?” የእግዚአብሔር መንግሥት የኢየሱስ ትምህርት ዋና ትኩረት ነበር። በመንፈሳዊነት ለማደግ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት መረዳት አለብን። የእግዚአብሔር መንግሥት መንፈሳዊ መንግሥት እንጂ በአሁኑ ዘመን ያለ ሥጋዊ መንግሥት አይደለም። ሆኖም፣ የእግዚአብሔር መንግሥት በዓለማችን ውስጥ አለ እና በብዙ መንገዶች ተጽዕኖ ያሳድራል። እርግጥ ነው፣ እያንዳንዱ መንግሥት መሪ ወይም ንጉሥ አለው። የእግዚአብሔር መንግሥት ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

      ዮሐንስ 3፡3 ኢየሱስም መልሶ፡— እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም፡ አለው።

      ሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማየት እና ለመግባት ዳግመኛ መወለድ ወይም መዳን አለበት። የእግዚአብሔር መንግሥት ዜጎች በኢየሱስ ብቻ ያመኑ ናቸው።

      ዳንኤል 2:44፣ በእነዚያም ነገሥታት ዘመን የሰማይ አምላክ ለዘላለም የማይፈርስ መንግሥት ያስነሣል፥ መንግሥቱም ለሌላ ሕዝብ አይሰጥም። እነዚያን መንግሥታት ሁሉ ያደቅቃቸዋል ወደ ፍጻሜአቸውም ያደርሳቸዋል ለዘላለምም ጸንቶ ይኖራል።

      ነቢዩ ዳንኤል የእግዚአብሔር መንግሥት የማይፈርስ ዘላለማዊ መንግሥት እንደሆነ ነግሮናል። መንግሥተ ሰማያት ሌላውን መንግሥት ያደቃል እና ያጠፋቸዋል። የእግዚአብሔርን መንግሥት የሚቃወመው መንፈሳዊ መንግሥት የሰይጣን መንግሥት ነው። የሰይጣን መንግሥት ዜጎች የማያምኑ ናቸው። የሰይጣን መንግሥት በዓለም ሥጋዊ መንግሥታት ላይ ትልቅ ተጽዕኖ አለው። ኢየሱስ እንድንጸልይ አስተምሮናል…

      ማቴዎስ 6:10፣ መንግሥትህ ትምጣ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን።

      የእግዚአብሔር መንግሥት በሰማይ ትገዛለች፣ በዚያ ምንም የሚወዳደሩ መንግሥታት የሉም። በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ በሰማይ እንደሆነው ፍጹም በሆነ መልኩ ተፈጽሟል። የእግዚአብሔር መንግሥት ወደዚህ ምድር እንድትመጣ በየዕለቱ መጸለይ አለብን። እናም የእግዚአብሔር ፈቃድ በሰማይ እንደሆነው ሁሉ እዚህም በምድር እንዲሆን መጸለይ አለብን።

      የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን መንግሥቱ የምታድግበት ዋና መንገድ ናት። የእግዚአብሔር መንግሥት የሚያድገው ሰዎችን ከሰይጣን መንግሥት በማዳን ነው። እኛ እንደ ቤተ ክርስቲያን ሰዎችን ስናድን መንግሥቱን እናሰፋዋለን። ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ ከዋና ዋና መንገዶች አንዱን አስተምሮናል።

      የሉቃስ ወንጌል 10፡9 በእርስዋም ያሉትን ድውዮችን ፈውሱና፦ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ቀረበች በሉአቸው።

      የታመሙትን ለመፈወስ የእግዚአብሔርን ኃይል ስናመጣ፣ መንግሥቱ ትቃረባለች። ሰዎች በኃጢአታቸው ተፈርዶባቸዋል፣ ንስሐ ገብተው ወንጌልን ሰምተው ኢየሱስን ሲቀበሉ ግን የእግዚአብሄር መንግስት እየጽፋፋች ትመጣለች። ዛሬ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ከኢየሱስ የበለጠ እንማራለን።

      የእግዚአብሔር መንግሥት እንዴት ያድጋል?

      የሉቃስ ወንጌል 13፡18 እርሱም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት ምን ትመስላለች፥ በምንስ አስመስላታለሁ?

      በወንጌሎች ውስጥ፣ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግሥት ምን እንደሚመስል ብዙ ታሪኮችን ወይም ምሳሌዎችን ሰጥቷል። የእግዚአብሔር መንግሥት እግዚአብሔር የሚገዛበት፣ ፈቃዱ የተደረገበት ግዛት ነው። ኢየሱስ ስለ መንግሥቱ የሚናገራቸው ታሪኮች ብዙውን ጊዜ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት የተሳሳተ አስተሳሰብን ለማስተካከል ነው። ኢየሱስ ስለ መንግሥቱ በማስተማር ብዙ ጊዜ አሳልፏል ምክንያቱም ይህ መንግሥት በጣም አስፈላጊ ነበር። ሆኖም ስለ መንግሥቱ ያስተማረው ትምህርት በብዙዎች ዘንድ ብዙ ጊዜ ችላ ተብለዋል፤ አሁንም ችላ እየተባለ ነው።

      የሉቃስ ወንጌል 13፡19 ሰው ወስዶ በአትክልቱ የጣላትን የሰናፍጭ ቅንጣት ትመስላለች፤ አደገችም ታላቅ ዛፍም ሆነች፥ የሰማይ ወፎችም በቅርንጫፎችዋ ሰፈሩ አለ።

      የሰናፍጭ ዘር ልክ እንደ አሸዋ ቅንጣት የሚያክል ከትንንሽ ዘሮች አንዱ ነው። ሆኖም ዘሩ ሲያበቅል እና ሲያድግ የሰናፍጭ ተክል ወይም ዛፉ እስከ ዘጠኝ ጫማ ቁመት ሊደርስ ይችላል። በቅርንጫፎቹ ውስጥ ወፎች ጎጆአቸውን ለመሥራት በቂ ነው። የኢየሱስ ነጥብ ምንድን ነው?

      ሰዎች ቃሉን መናገርና መመስከርን ለተናገሩት ሰውም መጸለይን በጣም ትንሽ ነገር አድርገው ይቆጥራሉ። የሰናፍጭ ዘር ባልዳነ ሰው ላይ የምሥክርነት ቃል ወይም ጸሎቶች ሊሆኑ ይችላሉ። የሰናፍጭ ዘር ለጌታ ቤተክርስቲያን የምትሰጡት አስራት ሊሆን ይችላል። በኢየሱስ ስም የሚደረገው ማንኛውም ነገር እንደ የሰናፍጭ ቅንጣት ይመስላል እና ብዙ ጊዜ በጣም ትንሽ ይመስላል። ነገር ግን፣ ኢየሱስ በጣም እንደሚያድግ እና ለብዙዎች በረከት እንደሚያመጣ ተናግሯል።

      ሉቃስ 13:20—21፣ ደግሞም፡— የእግዚአብሔርን መንግሥት በምን እመስለዋለሁ? አንዲት ሴት ወስዳ ሁሉም እስኪቦካ ድረስ በሦስት መስፈሪያ ዱቄት የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች አለ።

      ይህንን ታሪክ ለመረዳት ሶስት መለኪያ ዱቄት ወደ 50 ፓውንድ ዱቄት በጣም ትልቅ መለያ መሆኑን ማወቅ አለብን፤ ሴትየዋ በዱቄት ውስጥ የቀላቀለችው እርሾ በጣም ትንሽ ነበር፤ ሆኖም እርሾው ሙሉውን የዱቄት መጠን በማቡካት ዳቦ አመጣ። ይህ ታሪክ የሚያሳየን ምንም እንኳን መንግሥቱ ትንሽ ቢመስልም በዙሪያው ባሉት ሁሉ ላይ ትልቅ ተጽእኖ ይኖረዋል። የእግዚአብሔር መንግሥት ከትንሽ ወደ ትልቅ ያድጋል።

      በ1906 በአዙሳ ጎዳና የነበረው ታላቅ መነቃቃት የጀመረው በአንድ “ፍራንክ ባርትልማን” በተባለ ግለሰብ ነው። ይህ ሰው መነቃቃት ወደ ሎስ አንጀለስ እንዲመጣ ሲማልድ ነበር። ከዊልያም ሴይሞር ጋር የተደረገው የመጀመሪያው ስብሰባ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሲወድቅ ከ8 ሰዎች ጋር ብቻ ነበር። በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ውስጥ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ድነዋል፣ ተፈውሰዋል። እናም እጅግ በጣም ለማመን በሚከብድ ከተፈጥሮ በላይ በሆነ መንገድ ስዎች ሲድኑና የእግዚአብሄር መንግስት ሲሰፋ ታይቷል። የዚያ ትንሽ ጅምር ተጽእኖ በዓለም ዙሪያ በመቶ ሚሊዮኖች በሚቆጠሩ በመንፈስ ቅዱስ የተጠመቁ አማኞች በሁሉም የአለም ሀገራት ተሰራጭተዋል።

      ስለ መንግሥቱ እድገት ወደ እግዚአብሔር የምትጠራውን የአንድ ሰው ወይም የጥቂት ቡድን ወይም የአንድ ትንሽ ቤተ ክርስቲያን የመንግሥት ሥልጣን ትንሽ አድረገህ አትመልከት። እነዚህ የኢየሱስ አጫጭር ታሪኮች እርስዎን ባሉበት ቦታ እምነትን ወደ ልብዎ ያምጣ። የእግዚአብሔር ስጦታ ልክ እንደ ትንሽ የሰናፍጭ ቅንጣት ወይም ትንሽ እርሾ እንደሆነ ይሰማሃል? ስጦታህን ለእግዚአብሔር ስታቀርብ እርሱ ብዙዎችን ለመባረክ እንደሚያበዛው እመን።

      ወደ እግዚአብሄር መንግስት መግቢያው እንዴት ነው ?

      ሉቃስ 13:23—24፣ አንድ ሰውም፦ ጌታ ሆይ፥ የሚድኑ ጥቂቶች ናቸውን? አለው። እርሱም እንዲህ አላቸው፦
      በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ፤ እላችኋለሁና፥ ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም።

      ኢየሱስ “የሚድኑት ጥቂቶች ናቸውን ?” የሚለውን ጥያቄ አልመለሰም። በዚህ ምንባብ ውስጥ እርሱ ግን በማቴዎስ 7፡13 ላይ ያለውን ተመሳሳይ ጥያቄ ነው የመለሰው።

      ማቴዎስ 7፡13-14 “በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤
      ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።

      ስለዚህ፤ አዎ ከማይድኑት ጋር ሲነጻጸር፣፤ የዳኑት ጥቂቶች ይሆናሉ። ኢየሱስ እዚህ ጋር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት መንገዱ በጠባብ በር እንደሆነ ነግሮናል። በጠባቡ በር ለመግባት መጣር እንዳለብን ይነግረናል። መጣር የሚለው የግሪክ ቃል መታገል፣ በአትሌቲክስ ውድድር መሳተፍ ወይም መታገል ማለት ነው። ከታዋቂ እምነት በተቃራኒ ወደ ጠባብ በር ለመግባት እና ለመዳን ቀላል አይደለም። እንዲያውም፤ ብዙዎች ወደ ጠባቡ በር ለመግባት እንደሚሞክሩ፣ ነገር ግን እንደማያልፉት እና እንደማይገቡበት ኢየሱስ ነግሮናል።

      ሉቃስ 13:25፣ ባለቤቱ ተነሥቶ በሩን ከቈለፈ በኋላ፥ እናንተ በውጭ ቆማችሁ፦ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ ክፈትልን እያላችሁ በሩን ልታንኳኩ ትጀምራላችሁ እርሱም መልሶ፦ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም ይላችኋል።

      በዚህ ታሪክ ውስጥ ጠባብ በር ያለው ቤት፤ የቤቱ ጌታ ኢየሱስ ነው። ኢየሱስ ዳግም ሲመለስ ወይም ኢየሱስን ያላመነ ሰው ሲሞት፤ ያን ጊዜ ኢየሱስ ማን እንደሆነ ያውቃል። ልክ እንደዚያው ጠባብ በር ያለውን ቤት በር እያንኳኩ ለመግባት ይሞክራሉ፤ ነገር ግን በሩ በቋሚነት ከውስጥ ተዘግቷል። ኢየሱስ ከቤት ውስጥ ሆኖ መልስ ይሰጣል፤ ከወዴት እንደሆናችሁ አላውቃችሁም ይላል።

      ሉቃስ 13:27—28፣ እርሱም፦ እላችኋለሁ፥ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም፤ ሁላችሁ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ይላችኋል።
      አብርሃምንና ይስሐቅን ያዕቆብንም ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ባያችሁ ጊዜ፥ እናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ፥ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።

      ኢየሱስ በዚህ በምድር ህይወት በእርሱ ያላመኑትን ሰዎች እንደማያውቅ ደጋግሞ ተናግሯል። ክፉ አድራጊዎችም ይላቸዋል። የልቅሶ እና ጥርስ ማፋጨት ቦታ ውስጥ እንዳሉ በዘላለም ስቃይ ውስጥ እንደሚጣሉና ወደ ገሃነም እንደተላኩ ይናገራል።

      በኢየሱስ ዘመን እርሱን እንደ መሲህ ያልተቀበሉትን ሃይማኖተኛ አይሁዳውያንን እያነጋገረ ነበር። ሉቃስ 13:29—30፣ ከምሥራቅና ከምዕራብም ከሰሜንና ከደቡብም ይመጣሉ፥ በእግዚአብሔርም መንግሥት በማዕድ ይቀመጣሉ። እነሆም፥ ከኋለኞች ፊተኞች የሚሆኑ አሉ፥ ከፊተኞችም ኋለኞች የሚሆኑ አሉ።

      ኢየሱስ የሚናገረው በኢየሱስ የሚያምኑትን አሕዛብ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ እንደሚሆኑ ነው። በዚህ ዓለም የመጨረሻ የሚመስሉ ሰዎች፣ ማዕረግ ወይም ሀብት የሌላቸው፣ በመንግሥቱ የመጀመሪያ ይሆናሉ። ሌሎች በዚህ ዓለም የመጀመሪያ የሚመስሉ፣ በሥልጣንም ሆነ በሀብት የመጀመሪያ መሳዮች የመጨረሻ ይሆናሉ ይላል። በጠባቡ በር በመታገል ወደ መንግስቱ ይገባሉ።

      ቤተክርስቲያን ዛሬ ራሴን ጨምሮ አማኝ ለመሆን የወሰንንባትን እና ያቻልንበትን ያችን ቅጽበታዊ ጸሎት በጣም ቀላል እናደርጋታለን። በአንድ በኩል ቀላል ነው፣ ንስሀ መግባት እና በኢየሱስ ማመን ወደመንግስቱ ያስገባናል። ሆኖም፣ ብዙ ሰዎች ያንን ቀላል ጸሎት ይጸልያሉ ነገር ግን ህይወታቸውን ለጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ አይሰጡም አያስገዙምም። ከኢየሱስ ጋር ግንኙነት ለመጀመር በጣም ይታገላሉ።

      በህይወት ውስጥ አቧራማ በሆነ መንገድ ላይ ስለሚሄድ መንገደኛ ለአንድ ደቂቃ ያህል እናስብ። ትልቅ ቦርሳ አለው፤ ሌሎች ነገሮችን ደግሞ በቀበቶው እና በእጁ ይዞ እየተጓዘ ነው፤ ወደ ውብ የእግዚአብሔር መንግሥት ቤት ሲቃረብ እንኳን ደህና መጣችሁ የሚልብእጣም ደስ ይላል፤ እዚያ ገብቼ መደሰትና ማረፍ እፈልጋለሁ ብሎም ወደበሩ ቀረበ። በውስጡ በጣም የሚያስደስቱ እና የሚማርኩ ነገሮችን ተመለከተ። ነገር ግን በበሩ ውስጥ ለመግባት ሲሞክር በጣም ጠባብ መሆኑን ተገነዘበ፤ የቻለውን ያህል ሞክረ በተሸከመው ነገር ሁሉ በሩን ማለፍ አልቻለም። ይህ ግለሰብ የተሸከማቸው ነገሮች፤ ንብረቶቹ ገንዘቡን፣ ግንኙነቶቹን፣ ስራውን፣ ግቦቹን እና ኃጢአቶቹን ይወክላሉ።

      ሰውዬው አንዳንድ ነገሮችን ያስቀምጣል፤ ነገር ግን አሁንም በበሩ ውስጥ መግባት አልቻለም። በመጨረሻም በጠባቡ በር ለመግባት ያለውን ሁሉ መተው እንዳለበት ይገነዘባል። በሚያሳዝን ሁኔታ ንብረቶቹን እንደተሸከመ መግባት ስላልቻለ መንገዱን ይቀጥላል። በጠባቡ በር ለመግባት ሁሉንም ነገር አሳልፎ ለመስጠት ፈቃደኛ አይደለምና።

      ሆኖም ይህ ሰው አንዳንድ ነገሮችን አስቀምጧል፤ አልፎ ተርፎም አልፎ አልፎ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄዷልና አማኝ እንደሆነ ያስባል። ነገር ግን የእግዚአብሔር መንግሥት ዜጋ አይደለም። ጠባቡን በር አላለፈውም። ወደ ጠባብ የመንግስቱ በር ለመግባት ሁሉንም ነገር ማስቀመጥ ይጠይቃል።

      ከእግዚአብሔር መንግሥት የተገለለው ማን ነው?

      ሉቃስ 13:32፣ እንዲህም አላቸው፦ ሄዳችሁ ለዚያች ቀበሮ፦ እነሆ፥ ዛሬና ነገ አጋንንትን አወጣለሁ በሽተኞችንም እፈውሳለሁ፥ በሦስተኛውም ቀን እፈጸማለሁ በሉአት።

      ኢየሱስ ንጉሥ ሄሮድስን ያልጨነቀው ቀበሮ መሆኑን እየተናገረ ነው። ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ተልእኮ የመንግስቱ ስራ ላይ ነበር። አጋንንትን በማባረር እና ሰዎችን በመፈወስ የ እግዚአብሄርን መንግስትን ኃይል ማሳያዎች ወይም ምልክቶች እንደሆኑ ጠቅሷል። ኢየሱስ ለኃጢአታችን ሊሞት ወደ መስቀል እያመራ መሆኑን እና ጊዜው እንደቀረበ ያውቅ ነበር።

      ሉቃስ 13:34 ኢየሩሳሌም፥ ኢየሩሳሌም፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን በክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ፥ እናንተም አልወደዳችሁም።

      እየሩሳሌም የእስራኤል ዋና ከተማ ነበረች። ሆኖም ባለፉት መቶ ዘመናት ውስጥ እውነተኛ የእግዚአብሔር ነቢያት ተገድለዋል እና ተወግረው ነበር። ኢየሱስ ሁሉም የአይሁድ ህዝቦች እንደ መሲህ እንዲያምኑት ፈልጎ ነበር። ሆኖም፣ ንስሐ ለመግባት እና በኢየሱስ ለማመን ፈቃደኛ አልነበሩም። ስለዚህ፣ ባለማመናቸው የተነሳ፣ ከእግዚአብሔር መንግሥት ይገለላሉ ማለት ነው። ኢየሱስ በማያምኑት እስራኤል ላይ የእግዚአብሔርን ፍርድ ተናገረ።

      ሉቃስ 13:35፣ እነሆ፥ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል። እላችኋለሁም፥ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ ከእንግዲህ ወዲህ አታዩኝም።

      በታሪክ እንዳየነው ኢየሱስ ወደ አባቱ ካረገ ከ40 ዓመታት በኋላ፣ በ70 ዓ.ም.፣ ሮማውያን ቤተ መቅደሱንና የኢየሩሳሌምን ከተማ በሙሉ እንዳፈረሱት እናውቃለን። በኢየሱስ ዘመን እና በታሪክ ውስጥ፣ አብዛኞቹ አይሁዶች ኢየሱስን መሲህ እንደሆነ አላወቁም እና ወደ እግዚአብሔር መንግሥት አልገቡም ነበር። አንድ ቀን፣ ኢየሱስ ተመልሶ ይመጣል እናም ሁሉም አይሁዳዊም ጨምሮ ያዩታል። እርሱ ከመመለሱ በፊት በእርሱ የሚታመኑት ብቻ ይድናሉ ወደ እግዚአብሔር መንግሥትም ይገባሉ። በኢየሱስ ያላመኑት ከእግዚአብሔር መንግሥት የተገለሉ ናቸው።

      ከእግዚአብሔር መንግሥት የተገለሉት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የጨለማ ግዛት ተብሎ በተጠራው በሰይጣን መንግሥት ውስጥ ለዘላለም ይኖራሉ። ከገሃነም ማምለጥ የለም፤ በሲኦል ውስጥ የእግዚአብሔር መገኘት የለም፤ እንዲያውም፣ ኢየሱስ ከተናገራቸው ምሳሌዎች ውስጥ በገሃነም ውስጥ ያሉት ሰዎች ወደ መንግሥተ ሰማያት መመልከት እንደሚችሉ፣ ይህም ስቃዩ እንዲጨምርባቸው ያደርጋል። የእግዚአብሔርን መንግሥት ክፍል መምረጥ በህይወት ውስጥ በጣም አስፈላጊው ውሳኔ ነው።

      ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት ብቸኛው መንገድ ንስሐ መግባት እና በኢየሱስ ማመን ነው። ሁሉንም ነገር አስቀምጠህ በጠባቡ የመንግሥቱ በር መግባቱን ምረጥ። አንድ ሰው ኢየሱስን የማያውቅ ከሆነ፣ የመንግስቱ አካል አይደለም እና አልዳነም።

      የእግዚአብሔርን መንግስት መረዳት በህይወት ውስጥ በጣም አስፈላጊ ከሆኑ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነው። የእግዚአብሔር መንግሥት የኢየሱስ ትምህርት ዋና ነጥብ የሆነውም ለዚህ ነው። የእግዚአብሔርን ቃል ዘር ስንዘራ የእግዚአብሔር መንግሥት በዙሪያችን እያደገ ነው። ምንም እንኳን በሰዎች ህይወት ውስጥ በትንሹ ቢጀምርም፤ በትናንሽ ቡድኖች፤ አብያተ ክርስቲያናት ወይም ከተማዎች፤ በእግዚአብሔር ጸጋ ያድጋል።

      የመንግስቱ አካል ለመሆን በጠባቡ በር ለመግባት መታገል አለብህ። ያንንአልፎ ለመግባት ሁሉም ሰው ያለውን የተሸከመውን ሁሉ ማስቀመጥ አለበት። ሁሉንም ለኢየሱስ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑ ከመንግሥቱ ውጭ ይሆናሉ።

      ስለዚህ ይህንን መልእክት እያነበቡ እና ከመንግስቱ ውጭ መሆንዎትን እያወቁ ከሆነ እባክዎ ዛሬውኑ ወደዚህ መንግስት ለመግባት ይወስኑ። ወደመንግስቱ ለመግባት እና የዘላለምን ህይወት ለማግኘት ብቸኛውና አማራጭ የሌለው መንገድ ደግሞ፤ እርስዎን ለማዳን ስለሃጢያትዎ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ በመሞት፤ በመቀበር፤ በሶስተኛውም ቀን ከሞት በመነሳት፤ ወደመጣበት ወደ አብ መንግስት በማረግ፤ ደግሞ በክብር እመለሳለሁ እንዳለ፤ ዳግመኛ የሚመለሰውን ጌታ ኢየሱስን የህይወትዎ ጌታ እና አዳኝ አድርገው በመቀበልና፤ በእርሱ ጸንተው በመኖር ነውና ይህንን ያድርጉ። ጌታም ይረዳዎታል።

      ጆሮ ያለው ይስማ !

      ይህ የመጨረሻው ደውል የተሰኘው ድህረ ገጽ የማንቂያ ደውል እንደሆነም ያስቡ !

        ካሱ ቦስተን 

          ይህንን ጽሁፍ ወደውት ከሆነ ላይክ በማድረግ እንዲሁም ድህረ ገጹን ሰብስክራይብ ቢያደርጉ ሌሎች ጽሁፎች ሲለቀቁ ወዲያው እንዲደርስዎት ይሆናል። ለሌሎች በማካፈልም የድርሻዎትን ይወጡ።

      እንዲሁም ከታች ባሉት ሌሎች ዌብሳይቶች ላይ ያገኙኛል ሊንኩን በመጫን ይፈልጉኝ አመሰግናለሁ።

      https://youtu.be/LbCx7WVy3ZY

      linkedin.com/in/kassuboston

      https://www.tiktok.com/@kassuboston

      https://www.instagram.com/kasselsa97

      https://www.facebook.com/kasselsa97

      https://thelastbelldotcom.wordpress.com

      መልካም እረኝነት

      (የዮሐንስ ወንጌል 10:11) መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል

       (የዮሐንስ ወንጌል 10:14-15) መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።

      በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። (የሃዋርያት ሥራ 20፡28)

      እረኛ (የመጽሃፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 178) በጎችና ፍየሎችን ከብቶችንም የሚያሰማራ፤ የጠፋውን የሚፈልግ፤ ከአውሬዎች የሚጠብቅ በማለት ይፈታዋል።

      እረኛ ሕይወት ባለው መንጋ ላይ የሚሾም ነው፡፡

      እረኝነት በሁለት መንገድ ይታያል፦ አንዱ ቅጥር ሲሆን ሁለተኛው ሹመት ነው፡፡ (ቅጥር ህዝቡ ያስፈልገኛል ይሾምልኝ (ይቀጠርልኝ) ብሎ ልክ የእስራኤል ህዝብ ንጉስ ያስፈልገናል አንግስልን ብለው ሳሙኤልን እንዳስጨነቁና ሳኦል እንደነገሰላቸው ያለ አይነት ማለት ነው)። ሹመት ግን እግዚአብሄር ለህዝቡ ወይም በህዝቡ ላይ እረኛ ሲሾም (ይህ ግን በእግዚአብሄር ጥሪና በእግዚአብሄር ምሪት ለሚያስፈልገው ህዝብ እግዚአብሄር ሲሾም ነው)። 

      ሕይወት ያለው ነገር ተጠሪ ወይም እረኛ ያስፈልገዋል፡፡ ይህ ዓለም ሲዋቀር መሪና ተጠሪ ያለበት ዓለም ነው፡፡ ስለዚህ ሦስት ታላላቅ ተቋማት እረኛ ወይም መሪ አላቸው፡፡ ለቤተሰብ አባወራ፣ ለአገር ንጉሥ፣ ለቤተ ክርስቲያን አገልጋዩ እረኛው ናቸው፡፡ በዚህ አገላለጽ እረኛ ወይም መሪ ወደ መልካም ግብ የሚወስድ ንጉስ ወይም አባወራ ማለት ነው፡፡

      በእስራኤል አገር እረኛ ከፊት ለፊት ድምፁን እያሰማ የሚሄድ ሲሆን፤ በጐቹ የእረኛቸውን ድምጽ እየሰሙ ይከተሉታል፡፡ እረኛ ሁሌም ከፊት የሚቀድም ነው፡፡ እረኛው ሲቀድም መሪ ይሆናል፡፡ ከኋላ ከሆነ ነጂ ይሆናል፡፡ እረኛው ሲቀድም በዜማ መንጋውን ያስከትላል፡፡ ከኋላ ሲቀር ደግሞ በጅራፍና በዛቻ በማስፈራራት ይነዳል። የአገራችን እረኝነት መንጋው ከፊት እረኛው ከኋላ ነው፡፡ ይህ በብዙ የሕይወት መስክ ያለ ነባራዊ ችግራችን ይመስላል፡፡ በቤተ ክርስቲያን መሪዎቹ አይመሩም፤ ሣንቲም የሚጥለው ሕዝብ ይመራል፡፡

      እብራውያኖች ደግሞ መንጋዎቻቸውን በሰለጠነ ውሻ ያስጠብቁ ነበር። ለምስክር ይሆን ዘንድ ኢዮብ የነበሩትን ከብቶች በውሻ ያስጠብቅ እንደነበር መጽሃፍ ቅዱሳችን ያስረዳናል። (ኢዮብ 30፡1) እነዚህ ውሾች መንጋዎችን ወደ ለመለመ መስክ አይወስዱም፤ እረፍት ወደአለበት ውሃ ዘንድ አይመሩም፤ መንጎቹ ተሰብስበው ባሉበት ስፍራ መጠበቅ ይችሉ ይሆናል፤ ከመንጎቹም መሃከል ወጣ ለማለት የምትፈልገዋን እንስሳ በጩኸት ወይም በመናከስ ሊመልሷት ይችሉ ይሆናል። እረኛ የሚያስብል አንዳችም ባህሪ ኝ የላቸውም።

      መልካም እረኛ የእርሱ ያልሆነውን መንጋ በአደራ ተቀብሎ ከራሱ በላይ ይንከባከባቸዋል፡፡ መልካም እረኛ የሚያሲዘው ነገር ስለሌለ የገዛ ነፍሱን አስይዞ እረኛ ይሆናል፡፡ መልካም እረኛ ራሱን ካልሰጠ እረኛ አይሆንም፡፡ መልካም የተባለ እረኛ እንዳለ ሁሉ መልካም ያልተባለ እረኛም አለ።

      መልካም እረኛ፡

      1-     የእኔ የሚላቸውን ነገሮች አስቀምጦ ይጀምራል፡– መልካም እረኛ ሀብቱን፣ ሥልጣኑን፣ እውቀቱን፣ የኔ የሚላቸውን እንዲሁም እኔነቱን አስቀምጦ መጀመር አለበት፡፡ ራሱን የሰጠ፤ የኔ የሚለው አንዳችም ነገር የሌለው መሆን አለበት፡፡ ራሱን የሰጠ በሌላ አይታማምና፡፡

      2-    ዘመኑን ይሰጣል፡- መልካም እረኛ ቀን ከመንጋው ጋር ይውላል፡፡ መንጋው ቀኑን በሙሉ ይበላል እርሱ ግን ጦሙን ሊውል ይችላል፡፡ ማታም በበረቱ ውስጥ ቆጥ ላይ ያርፋል፡፡ እረኛ ማለት ለቅጽበት ከመንጋው የማይለይ ነው፡፡ ስለዚህ እረኛ ዘመኑን ለመንጋው የሰጠ ነው፡፡ እንዲሁም እረኛ የዘመኑን ሽራፊ፣ የጊዜውን ጭላጭ ሳይሆን የዕድሜውን አስኳል ሊሰጥ ይገባዋል፡፡ እረኛ እንደ ኮንትራት ሠራተኛ፣ የሚሻውን ሲያገኝ የሚታጠፍ አይደለም፡፡ እረኝነት ቀን መግፊያ፣ የሚፈልጉትን ጉዳይ መጠበቂያ አይደለም፡፡ እረኛ አገልግሎቱ ለተፈጠረበት ዓላማ የሚጓዝበት ግብ ያለው ነው፡፡ እረኛ መላ ዘመኑን መስጠት፣ ከመንጋው ጋርም ያለ ማቋረጥ መገናኘት አለበት፡፡

      3-  ከአራዊት ይናጠቃል፡- እረኛ የራሱን ሕይወት አደጋ ላይ ጥሎ መንጋውን ከአውሬ ያስጥላል፡፡ እንዲሁም ከአጋንንት፣ ከዓለም ምእመናንን መታደግ የተሰጠው የስራ ድርሻው ነው፡፡ ከአውሬ ሲያስጥል መቊሰሉ አይቀርም፡፡ ከእሳት ሲያወጣ መለብለቡ አይቀርም፡፡ በዚህ ጊዜ በጐቹ የተከፈለላቸውን ዋጋ አያውቁትም፣ ላያመሰግኑትም ይችላሉ፡፡ እረኛው ግን ለመንጋው ሲል ይህን ሁሉ ማድረግ አለበት፡፡ አዎ እረኛ ለመሆን ራስን መስጠት ግድ ይላል፡፡ ምክንያቱም መያዣው ነፍስ ነው፣ ዳግመኛም ዘመንን መስጠት ይጠይቃል፣ ከአራዊት ጋር መታገልም ያስፈልገዋል፡፡ መልካም እረኛ የሆነ ራሱን መስጠት ካልቻለ መንጋውን ለመጠበቅም ሆነ ለመመገብ አይችልም፡፡ የእረኝነት ቊልፉ ራስን መስጠት ነውና፡፡

      ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ እረኛ በሆነ ጊዜ የፈረመው በደሙ ነው፡፡ የዕብራውያን መልእክት ፀሐፊ፡- “በዘላለም ኪዳን ደም ለበጎች ትልቅ እረኛ የሆነውን …. ይላል (13÷20)፡፡

      ጌታችን የሕይወታችን ብቻ ሳይሆን የአገልግሎታችንም አርአያችን (ሞዴላችን) ነው፡፡ ጌታችን የልደቱን ምሥጢር ለካህናት ሳይሆን ለእረኞች መግለጡ የእረኞች አለቃነቱን ይሣያል፡፡ በዘመናትም ታላላቅ ምሥጢራት የተገለጡት ለእረኞች ነው፡፡ ያዕቆብ፣ ዳዊት እረኞች ነበሩ፡፡ ዳዊትን ስንመለከት የሚጠብቃቸውን በጎች ለራሱ ነፍስ ሳይሳሳ ከአውሬ አፍ መንጭቆ የሚያወጣ ነበር።  

      በሌላ መልኩ የበጎችን በረት የሚጠብቅ (ሌላ እረኛ መሳይ) የተቀጠረ፤ በር ላይ የሚቆም፤ ጠባቂ ብቻ የሆነ በበረቱ ውስት ያሉት በጎች ሁሉ የራሱ ያልሆነ፤ ለበጎቹ ግድ የሌለው፤ ደግሞ ጠባቂ ወይም ተቀጣሪ የሚባል መልካም ያልሆነ እረኛ፤ በጎቹን ሊተናኮል የሚመጣ አውሬ ቢመጣ ትቶ የሚሸሽ አይነት፤ ህይወቱን ለበጎቹ ሲል አሳልፎ ሊሰጥ የማይችል አይነት፤ ተቀጣሪ ወይም በር ላይ ብቻ ሆኖ የሚጠብቅ ጠባቂ እረኛ አለ።

      ሃዋርያው ጳውሎስ ለቤተክርስቲያን መሪዎች መመሪያ ሲሰጥ መልካም መሪዎች ማለትም እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም እረኞች ሆነው በክርስቶስ የተዋጀውን ህዝብ ይጠብቁ ዘንድ፤ የርሱን አርዓያ ይከተሉ ዘንድ አዟል። እንዲህ በማለት ” በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። (የሃዋርያት ሥራ 20፡28)” መልካም እረኝነትን ለጌታ ለኢየሱስ ብቻ የተሰጠ አድርገን እንዳንመለከት በተለይ ቤተክርስቲያንን (የጌታን ህዝብ) ለመምራት በሃላፊነት ላይ ያለን መሪዎች የርሱን ምሳሌ እንድንወስድ ታዘናል። መልካም እረኛችን እርሱ ብቻ ነው እንደእርሱ ያለ መልካም እረኛ የለንም በማለት፤ ለእኛ የተሰጠንን ህዝቡን የመጠበቅ እና የመምራት ሃላፊነት ወደጎን ተወት ያደረግን እንደሆን የእረኞች እረኛ የሆነው ጌታ ይጠይቀናል።

      በዘመናችን ያየናቸው እረኞች ሶስት አይነቶች ናቸው፦   

      1.             የመንጋው ባለቤት

      2.            የመንጋው እረኛ

      3.            የመንጋው ነጋዴ 

      1-   የመንጋው ባለቤት፡–  እረኞች የመንጋው ባለቤት ለመሆን ይዳዳቸዋል። እረኞች መንጋውን የሚጠብቁ፣ የሚንከባከቡ የሚመግቡ እና የሚያሳድጉ ባለ አደራዎች እንጂ ባለቤት አይደሉም፡፡ የመንጋው ባለቤት እግዚአብሔር ነው፡፡ ሾልከው የገቡ እረኞች እንዲህ አይነት ባህሪ ይታይባቸዋል። 

      2-   የመንጋው እረኛ፡–  የእረኝነት ልብና ጥሪ ያለው እርሱ የመንጋው እረኛ ይባላል። እንዲህ አይነት እረኛ መንጋዎቹ ሊያወሩት የሚፈልጉት፣ እርሱም ሁሉን ለመስማት የልብ ስፋት ያለው፣ ማስተማር፣ መምከር የመንጋውን ጤንነት መቆጣጠር የሚችል እርሱ የእረኝነት ጸጋ ያለው ነው፡፡ እረኛ የመንጋውን ባለቤት እያሰበ የተሰጠውን አደራ ለመወጣት ይጥራል፡፡ ሕዝቡ የእግዚአብሔር ነው ብሎ፣ በደም ዋጋ የተገዛ የክርስቶስ ገንዘብ መሆኑን አስቦ የተሰጠውን አደራ ለመፈጸም ጠንቃቃ ይሆናል፡፡

      3-   የመንጋው ነጋዴ፡– የመንጋው ነጋዴ እረኞች መንጋውን የሚፈልጉት ለሥጋዊ ጥቅማቸው ብቻ ነው፡፡ የመንጋው ነጋዴዎች መንጋውን ሲመለከቱትም ሆነ ሲመግቡት መንጋው ከተመገበ በኋላ አድጎ ለእርድ እንዲደርስ ብቻ ያሳድጉታል፤ ከዚያም ሥጋው ይህን ያህል ቆዳው ይህን ያህል ያወጣል እያሉ ከመንጋው የሚያገኙትን ትርፍ ሲያሰሉና ሲተምኑ፤ ከመንጋው የሚያገኙትን ገቢ ሰብሳቢዎች ሆነው ይቀራሉ። ትርፍ ካስገኘላቸውም ደግሞ ለሌላ በላተኛ አሳልፈው ከመስጠትና ከመሸጥ ወደኋላ አይመለሱም። እነዚህ የመንጋው ነጋዴዎችም ሆኑ መንጋውን በባለቤትነት ለመያዝ የሚፈልጉ እረኞች ሌላ ስፍራ ላይ የሚያገኙት ጥቅም ካጋጠማቸው ወይም ደግሞ መንጋው የሚረባ(የሚወልድ/የሚበዛ) ወይም ዋጋ የሚያወጣ ካልመሰላቸው፤ መንጋውን ቀን ያሰማሩበት ሜዳ ላይ በትነውት መንጋው በአውሬ ይበላ አይበላ፤ ሲመሽ ወደ ማደሪያው በረት ይግባ አይግባ ግድ ሳይሰጣቸው/ሳይላቸው የሚፈረጥጡ አይነቶች ናቸው።    

      የእረኛ ባሕርያት (መገለጫዎች)

      1.    መጋቢ ነው፡– እረኛ ለምለሙን ሣር፣ ንጹሑን ውሃ እየፈለገ መንጋውን ይመግባል፡፡ አገልጋይም የጠራውን ቃለ እግዚአብሔር፣ ጤናማውን ትምህርት በመስጠት የምእመናንን ነፍስ ይመግባል፡፡

      2.   ጠባቂ ነው፡– እረኛ በጐቹን ከራሳቸው ሞኝነትና ከጨካኝ አውሬ ይጠብቃል፡፡ መጠበቅ አድካሚ መሆኑን የሚያውቅ መሆን አለበት፡፡ ምእመናን ያለባቸው ፈተና ሰይጣናዊ ብቻ አይደለም፣ የገዛ ሞኝነታቸውም ፈተናቸው እንደሆነ አውቆ ከራሳቸውም ሞኝነት ይጠብቃቸዋል፡፡

      3.   አካሚ ነው፡– እረኛ ገደል ገብታ የወደቀችውን ያወጣታል፣ ስብራቷን ይጠግናል፣ መራመድ ቢያቅታት ይሸከማታል፡፡ አገልጋይም በስህተትም ሆነ በድፍረት ለወደቁት ምእመናን ይራራል፡፡ ካሉበት ድረስ ሄዶም ሐፍረታቸውን ገፎ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመልሳቸዋል፡፡

      4.    አመጣጣኝ ነው፡– እረኛ ብርቱው ደካማውን እንዳይገፋው፣ ግልገሎች ከትልልቆች ጋር ሲጓዙ ኋላ እንዳይቀሩ ያመጣጥናል፡፡ ሁሉንም በእኩልነት መመገብ፣ ደካማና ብርቱውን በማያያዝ አብረው እንዲራመዱ አመጣጥኖ ያስኬዳል፡፡ ብርቱውን ብቻ የሚከተል ደካማውን ወደኋላ የሚተው እረኛ መሆን አይችልም፡፡

      5.   መሸከም፡– እረኛ የተሰበረችውንና ፍጥነት የሌላትን ግልግል ይሸከማል፡፡ አገልጋይም ብዙ ማባበል የሚፈልጉትን ምእመናንን መታገሥ፣ ዕድገታቸው ዘገምተኛ የሆኑትን በተስፋ መጠበቅ ይጠበቅበታል፡፡ ሙሴ የሕዝቡን ድካም፣ ሸክም፣ ክርክር ተሸክሞ ነበር የሚመራው (ዘዳ. 1÷12)፡፡

      6.  ማሰማራት፡– እረኛ መንጋውን ያሰማራል፡፡ በቅርብ ርቀት ሆኖ ይከታተላቸዋል፡፡ አገልጋይ እረኛም ምእመናንን ማሰማራት፣ ሥራ መስጠት፣ እንዲያገለግሉ ማበረታታት አለበት፡፡

      7.  ስለ አንድ ይቆረቆራል፡– እረኛ ዘጠና ዘጠኝ በጐች ቢኖሩትና አንዲቱ ብትጠፋበት የሚበዛውን አትርፌአለሁ ብሎ አይተዋትም፡፡ ይፈልጋታል፡፡ አገልጋይም ስለ አንድ ነፍስ ግድ ሊለው ይገባል፡፡ የአንድ ነፍስ ዋጋን ያላወቀ አገልጋይ እረኛ ሊሆን አይችልም፡፡ የብዙዎችም ዋጋ የክርስቶስ ደም ነው፣ የአንዲቱም ዋጋ ያው የክርስቶስ ደም ነው፡፡

      8. በህብረት ይሰራል፦ እረኛ መንጎቹ በዝተው ለቁጥጥር እንዳያስቸግሩት መንጎቹን ከሚወዱና ከሚንከባከቡ ጋር አብሮ በመተባበር ይሰራል (ሙሴ በዘዳ 1፡12 ላይ ብቻውን ለመስራት ስላልቻለ ከምትመርጡት ሰዎች ጋር አብረን እንሰራልንና ሰዎችን ምረጡ አለ)

      ማጠቃለያ

      ጌታ ኢየሱስ ትልቅነት ማለት አገልጋይነት መሆኑን በተግባር ያሳየ መምህር ነው። ጌታ ኢየሱስ ሁሉም በእግሮቹ ስር የተገዙለት ጌታ ነው። እርሱ ጌታ ሆኖ ሳለ የኖረው ኝ እንደ አገልጋይ ነው። ትልቅነት ማለት አገልጋይነት እንደሆነ በኑሮው የገለጸ፤ የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠብ የዝቅተኝነትን ምሳሌነት ያሳየ እና ለደቀመዛሙርቱም የነገራቸው እርሱ እግር እንዳጠበ እነርሱም እግር እንዲያጥቡ ነው። ይህም “የአገልጋይነት” የዘወትር ልብሳቸው እንዲሆን ነው። መቼም ለእራት ከተሰበሰቡት መካከል እግር የማጠብ ተግባር የመምህሩ አይሆንም፤ የሌሎቹንም እግር እንዲያጥብ አይጠበቅበትም። ጌታና መምህር የሆነው ኢየሱስ “ለባሪያ/አገልጋይ” የ’ሚ’ተውን (‘‘ ጠበቅ ተደርጎ የሚነበብ) ስራ በመስራት የመሪነትን ምንነት በተግባር ያሳየ አስተማሪ ነው።

      ጌታን በሚከተሉ ደቀመዛሙርት መካከል ማን ትልቅ እንደሆነ እርስ በርስ የተከራከሩበት ጊዜ ነበር። ጌታም “ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፤ ከእናንተ ማንም ፊተኛ ሊሆን የሚወድ የእናንተ ባሪያ ይሁን፤” ነበር ያላቸው።

      በሌላ በኩል ደግሞ ስንመለከት፤ የጌታ አመራርና ጥበቃ ያተኮረው በቁጥር ብዛት ወይም በአብላጫ ላይ ሳይሆን በነፍስ ወከፍ ጥንቃቄ በማድረግ ላይ ነበር። በበረት ውስጥ ካሉት በጎች አንዱ ቢጠፋ ከዘጠና ዘጠኙ አንጻር “ምንም” ባልሆነ ነበር። ጌታ ኝ ለአንዱ የሚጠነቀቅና እስኪያገኘው ድረስ የሚፈልግ እረኛ ነው።

      ሰው በእግዚአብሄር አምሳል የተፈጠረና ከእርሱ ጋር ኅብረት እንዲያደርግ የተፈጠረ ክቡር ፍጥረት በመሆኑ ከአምላኩ ርቆ ሊባዝንና ሊጠፋ አይገባውም ብሎ ፍለጋ መሄድ የእረኝነት ባህሪ ነው። እረኛ በበረት “የቀረው ይበቃኛል” የሚል ሳይሆን አንዱን የጠፋውን ፍለጋ እንደሚሄድ “ሁሉም ለጌታ ያስፈልጉታል” (ማቲ 18፡12 እስከ14) የሚል ሰው ነው። መልካም እረኛ በተሰማራበት ቦታ ሁሉ ለሰው ዋጋ የሚሰጥ፤ ለአንድ ለባዘነ፤ ለደከመ፤ ለጠፋ ግድ የሚለው ነው። በአንጻሩ ደካሞችን የሚያገል(የሚያሸሽ) ወይም በመጥፋታቸው የሚደሰትና ጥቂቶቹን ብቻ በታጠረ በረት ውስጥ ቆልፎ የሚይዝ መሪ የመልካሙ እረኛ የኢየሱስ ክርስቶስ ልብ ያለው አይደለም።

      ጌታ ሲናገር “በጎቼ ድምጼን ይሰማሉ” (ዮሃ 10፡27) አለ። እንዲሁም ስለመልካም እረኛ ሲያስተምር፡ “በጎቹም ድምጹን ይሰሙታል፤ የርሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱን ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፤ በጎቹም ድምጹን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም። የሌሎችን ድምጽ አያውቁምና” (ዮሃ 10፡3 እስከ 5) አለ። ይህ በእረኛና በበጎች መካከል ያለውን መተዋወቅ፤ መቀራረብ፤ መተማመን ይገልጻል። እንዲሁም መሪ የሚመራውን ህዝብ የሚያውቅ ህዝቡም በአመራሩ በመተማመን የሚከተለው መሆን አለበት።

      የመልካሙ እረኛ የኢየሱስ ክርስቶስን ምሳሌነት የሚከተል እረኛ በጎቹን በስም የሚያውቅና ከበረት የጎደሉም ሲኖሩ እንዲመለሱ ፈጥኖ የሚፈልግ ነው። በጎቹም ወደበረት እንዲመለሱ አስቀድመው የመሪውን ድምጽ የሚያውቁ ሊሆኑ ይገባል። ስለሆነም በመሪውና በተመሪዎች መካከል፤ በእረኛውና በበጎች መካከል የቀረበ ኝኙነትና ትውውቅ አስፈላጊ ነው።

      በአጠቃላይ ክርስቲያናዊ መሪነት መልካም እረኝነት የሚሆነው የጠፋው በተገኘ ጊዜ፤ የባዘነው በተመለሰ ጊዜ፤ የደከመው በተጽናና ጊዜ ነው። እንዲህ አይነቱ መሪ የክርስቶስ ልብ ያለው የባዘኑትን ፈልጎ የሚያገኝ ደስታውም በመመለሳቸው የሚሆንለት ሰው ነው። እግዚአብሄር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም የተዋጁትን ልጆቼ ያላቸውን ህዝቦቹን ለተቀጣሪ እረኛ አሳልፎ አይሰጥም፤ በአደራ የተቀበለውን ህዝብ፤ በበረቱ ውስጥ የገቡትን መንጋዎቹን (በጎችን፤ ጥቦቶችን እና ግልገሎችን) እንደራሱ ለማይመለከት፤ የጠባቂነት መንፈስ ብቻ ላለው ተቀጣሪ እረኛ አሳልፎ አይሰጥም። ኢዮብ መንጋዎቹን በውሾች (ኢዮብ 30፡1) ያስጠብቅ እንደነበረውም እግዚአብሄር ህዝቡን ለጯሂና ለተናካሽ ውሾችም አይሰጥም። አይተውምም።

      መልካም እረኞችን ለማግኘት ምን እናድርግ ?

      ቃሉ፡“ብዙ ሕዝብም ባየ ጊዜ እረኛ እንደ ሌላቸው በጐች ተጨንቀው ተጥለውም ነበርና አዘነላቸው፡፡ በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡- መከሩስ ብዙ ነው፣ ሠራተኞች ግን  ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት አላቸው” ይላል (ማቴ. 9÷36-38)፡፡

      የጌታችን ታላቅ ሀዘንና ታላቅ መመሪያ ነው፡፡ ሀዘኑ እረኛ አልባ መሆናቸው ነው፣ መፍትሄው መልካም እረኛ እንዲሰጥ እግዚአብሔርን መለመን፣ መጠየቅ፣ ማንኳኳት፣ ሁሌም ሳይታክቱ መጮህ ነው፡፡ እረኛ የሌለው መንጋ የሚባዝን፣ የማይሰባሰብ፣ ድንጉጥ ነው፡፡ ከመንጋው ፊት የሚሆኑ ቀድመው የሚታዩ እረኞች ያስፈልጉናል፡፡ እረኛ የሚገኘው ደግሞ ምእመናን ሲጸልዩ ከምእመናን ውስጥ ነው፡፡ ከልብ ካልጸለዩ መልካም እረኞች አይነሡም፡፡ መጨረሻው በመንጋው ነጋዴዎች መወረር ይሆናል፡፡

      ምእመን ዛሬ ከፊት ከፊት እየሄዱ ስለሚመሩ ስለ መልካም እረኞች እየጸለይን ይሆን?

      እረኞችስ ድርሻችንን እየተወጣን ይሆን ? የመንጋው ባለቤት ያያል ! ለእያንዳንዱ እንደስራው መጠን የሚከፍል ዋጋው በእርሱ ዘንድ ያለ ጌታ በቶሎ እመጣለሁ ይላል !

      ጆሮ ያለው ይስማ !

      ይህንን ጽሁፍ ወደውት ከሆነ ላይክ በማድረግ እንዲሁም ድህረ ገጹን ሰብስክራይብ ቢያደርጉ ሌሎች ጽሁፎች ሲለቀቁ ወዲያው እንዲደርስዎት ይሆናል። ለሌሎች በማካፈልም የድርሻዎትን ይወጡ። እንዲሁም ከታች ያሉት ዌብሳይቶች ላይ ያገኙኛል ሊንኩን በመጫን ይፈልጉኝ አመሰግናለሁ።

      የሚያስተራርቁ (የሚታረቁ) ብጹዓን ናቸው !

      ከላይ በርዕሴ ላይ እንደምታዩት (በማቲዎስ ወንጌል 5፡9) የተራራው ስብከት ላይ የተገለጹትን ማለትም የብጽዕና መስፈርቶችን መዳሰስ ፈለግሁና ብጹዓን ናቸው ብሎ ጌታ ኢየሱስ የገለጻቸውን ሰዎች ማንነት ውስጥ እራሳችንን እንድንፈትሽና እንድናይ አንዷን አውጥቼ እንድናያት ፈለግሁ። 

            የጌታ ደቀመዝሙር ሰዎችን ለማስታረቅና ሰላምን ለመፍጠር የተጠራ አገልጋይ ነው። ጌታ ኢየሱስ ሰዎችን ከእግዚአብሄር ጋር፤ ሰዎችን ከሰዎች ጋር እና ሰዎችን ከራሳቸው ጋር በማስታረቅ ሰላም የሚያደርጉትን፤ እነዚህን የእግዚአብሄር ልጆች ይባላሉ ብሎ ገልጾአቸዋል። ስለዚህ የእግዚአብሄር ልጆች ከሆንን ይህንን ተግባር ለማድረግ መጣር አለብን እላለሁ። ዛሬ ዛሬ እንደምናየውና እንደምንመለከተው ግን በምንኖርበት አካባቢ ከእግዚአብሄርና ከሰዎች ጋር ሰላም አጥተን የምንኖር ብዙዎች ነን። የተጠራነው እርቅ እንድንፈጥርና ሰላምን እንድናወርድ ነው። የብጽዕና ህይወት መገለጫችን ሰላምንና እርቅን መፍጠራችን ነውና። አለበለዚያ የተባለው ተቃራኒ (የእግዚአብሄር ልጆች) አይባሉም ይሆናል። 

         አሁን እየታየ ያለውን የደቀመዛሙርትነት ህይወታችንን ስንመረምረው ግን፤ ለሰላምና ለእርቅ የተጠራን፤ እርስ በርሳችን ተከፋፍተንና ተከፋፍለን ለእርቅና ለግልግል ማስቸገራችንን ላየ ትዝብት ውስጥ ሳይከተን አይቀርም እላለሁ።  ዓለምን ከእግዚአብሄር ጋር ለማስታረቅ የተጠራች ቤተክርስቲያን፤ እርስ በርስ ተጣልታ እንድታስታርቀው በተላከችበት ዓለም፤ በተቃራኒው ለእርቅ ግልግል ውስጥ መግባቷ፤ ብጽዕናዋን እንዳታገኝ ያደርጋታል። ከብዙ ትግል በኋላ እንኳን የመታረቅ ሂደት ውስጥ ስትገባም  “እታረቃለሁ፤ ግን እንደድሮው አልሆንም” በማለት የታረቁ የሚመስሉ ግን ያልታረቁ ቤተክርስቲያን(ክርስቲያኖች)፤ አማንያን ወይም ደቀመዛሙርት መሆናችንን እንደውም ድንበርና ደንብ መተዳደሪያ አበጅተን የተቀመጥን እንዳለን ቤቱ ይቁጠረው።

         ዛሬም እንደፈርኦን ልባችንን አደንድነን በመቀመጣችን፤ የምድር ሁሉ ቀውስ ውስጥ መግባት ወይም አለመቆም ምክኒያት ሆነን ቢሆንስ ? እላለሁ ።     ጆሮ ያለው ይስማ !!    

      ተባረኩልኝ።  

      ካሱ ቦስተን 

      linkedin.com/in/kassuboston

      https://www.instagram.com/kasselsa97

      https://www.facebook.com/kasselsa97

        ቅዱሳን ሁኑ !

       ዳሩ ግን፦ እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት1:15-16

      ​(ትንቢተ ሕዝቅኤል 36:20-23)

      ወደ መጡባቸውም ወደ አሕዛብ በመጡ ጊዜ፥ ሰዎች እነርሱን፦ ከምድሩ የወጡ የእግዚአብሔር ሕዝብ እነዚህ ናቸው ሲሉአቸው ቅዱስ ስሜን አረከሱ። እኔ ግን የእስራኤል ቤት በመጡባቸው በአሕዛብ መካከል ስላረከሱት ስለ ቅዱስ ስሜ ስል ራራሁላቸው። ስለዚህ ለእስራኤል ቤት እንዲህ በል፦ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ በመጣችሁባቸው በአሕዛብ መካከል ስላረከሳችሁት ስለ ቅዱስ ስሜ ነው እንጂ ስለ እናንተ የምሠራ አይደለሁም። በአሕዛብም ዘንድ የረከሰውን፥ በመካከላቸው ያረከሳችሁትን ስሜን እቀድሰዋለሁ፤ በዓይናቸውም ዘንድ በተቀደስሁባችሁ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ አሕዛብ ያውቃሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፡፡

           እግዚአብሄር እኔ በአህዛብ ፊት እናንተን ከነርሱ ውጡና የተለያችሁ ሁኑ እርኩሱንም ነገር አትንኩ ብያችሁ ነበር ነገር ግን እናንተ በመሃከላቸው ሆናችሁ ቅዱሱን ስሜን አረከሳችሁት: ስለዚህ እኔ እንደሎጥ እራራላችሁና እጃችሁን ይዤ አወጣችኋለሁ ለራሴ ለቅዱሱ ስሜ ስል እቀድሳችኋለሁ: ያኔ እናንተን ስቀድስ መልካም አድርጌ ስሠራችሁና በናንተ ውስጥ ስኖር አህዛብ እኔ እግዚአብሄር እንደሆንኩ ያውቃሉ እኔ እራሴ ስሜን አስከብራለሁ እናንተን እቀድሳለሁ እንደገናም በእናንተ እቀደሳለሁ ይላል ይህን የማደርገው ግን እናንተ ስለሰራችሁት ስለመልካም ስራችሁ ሳይሆን ስለራሴ ቅዱስ ስለሆነው ስሜ ነው ይላል ምክኒያቱም እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን እንድትሆኑ ስለምፈልግና እኔንም ማየት የምትችሉት በቅድስና ስትኖሩ ስለሆነ ነው፡፡

         እንግዲህ መንፈሳዊ ቤት ሆናችሁ እንድትሰሩና እኔ እንድኖርባችሁ ይህን ከዚህ የሚቀጥለውን በመካከላችሁ አደርጋለሁ ይላል እግዚአብሄር፡፡

           ከአሕዛብም መካከል አወጣችኋለሁ፥ ከየአገሩም ሁሉ እሰበስባችኋለሁ፥ ወደ ገዛ ምድራችሁም አመጣችኋለሁ። ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ፥ እናንተም ትጠራላችሁ፥ ከርኵሰታችሁም ሁሉ ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ። አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ፥ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ፥ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ። መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ፥ በትእዛዜም አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ። ለአባቶቻችሁም በሰጠኋት ምድር ትኖራላችሁ፤ ሕዝብም ትሆኑኛላችሁ እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ። (ትንቢተ ሕዝቅኤል 36:24-28) አሜን አሜን አሜን!!!

      kasselsa97

      https://youtu.be/LbCx7WVy3ZY

      https://www.tiktok.com/@kassuboston

      linkedin.com/in/kassuboston

      “ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ”

      መጽሃፍ ቅዱስ በዕብራውያን 12:14 ላይ (ህያው ቃል ከተሰኘው መጽሃፍ ቅዱስ የተወሰደ) “ከማንም ሰው ጋር ተስማምታችሁ በሰላም ኑሩ ቅድስና የተሞላበትንም ህይወት ለመኖር ፈልጉ ምክኒያቱም ያለቅድስና ህይወት ጌታን ማየት ፈጽሞ አይቻልምና ” በማለት ያሰፈረው ቃል ላይ ቅድስና የተሞላበት ህይወት ለመኖር ፈልጉ ሲለን ይህ ሃሳብ ጌታ ኢየሱስን እንደግል አዳኛችን አድርገን ከተቀበልንበት ጊዜ ጀምሮ ያለውና ወደፊትም የምንኖረው ህይወት በቅድስና ህይወት ይሁን ነው እያለን ያለው።

          ቅድስና ከደህንነታችን ቀጥሎ ትልቅ ግምት ልንሰጠው የሚገባ የህይወት ክፍላችን ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የበደላችንንና የሃጢዓታችንን ዋጋ ከከፈለ በኋላ በዕምነት ወደ እርሱ ቀርበን የጽድቁ ተካፋይ እንሆን ዘንድ ተጋብዘናል ግብዣውንም ተቀብለን በጸጋው የጽድቁ ተካፋዮች ሆነናል። ይህ ማለት ግን በምድር የሚኖረንን የቅድስናና የጽድቅ ህይወት ፈጽመን አበቃን እንደፈለግን እንኑር ማለት ግን አይደለም ይልቁንም ጀመርነው እንጂ።  

          ቅድስና በአንድ ቀን አዳር ወይም በአንድ ቀን ጸሎት የምንከውነው ሳይሆን የእድሜ ልክ ልምምድና ኑሮ መሆኑን ልንገነዘበው ይገባናል። ለዚህ ነው የእግዚአብሄር ቃል “ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ” የሚለን በአጭር መንገድ ተጉዘን ቅድስናን አግኝተን ጨርሰነዋል ማለት ሳይሆን ሳንታክት ሳናቋርጥ ዘወትር በጽናትና በትዕግስት የምንፈልገውና የምንፈጽመው ወደተሰጠንም ወደ እግዚአብሄር ክብር የምንተላለፍበት ብቸኛው መንገድ ነውና ሳንታክት በቅድስናና በንጽህና ለመኖር እንፈልግ ብዬ የዛሬውን መልዕክቴን በዚሁ አጠናቅቃለሁ። ተባረኩ ።

      ካሱ ቦስተን

      kasselsa97

      https://youtu.be/LbCx7WVy3ZY

      https://www.tiktok.com/@kassuboston

      linkedin.com/in/kassuboston

      የዘላለም ህይወት እንዳለን እርግጠኛ ነን ?

      ክፍል 6

      የእግዚአብሔር ልጅ መሆን !

      በክፍል 5 ንባባችን ላይ ክርስቶስ ቅጣታችንን እንደተቀበለ ተመልክተናል። ክርስቶስ ስለእኛ ሲል በመስቀል ላይ እስከሞት ድረስ ያደረሰው እግዚአብሄር ለእኛ ያለውን ታላቅ ፍቅር መግለጫ እንደሆነ እናስተውል፤ በሌላ መልኩ ደግሞ ስንመለከተው አንድ የሚያስገኝልን ትልቅ የእግዚአብሄር ልጅነት ስልጣን ነው። በመስቀል ላይ የሞተልንን ጌታ ኢየሱስን አምነን የዘላለም ህይወት ወራሽ ከመሆናችን ጋር የምንወርሰው የልጅነት ስልጣን እንደሆነ በገላቲያ 3፡26-27 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤››፡፡ ሁላችን የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን ፍላጎት ቢኖረንም ይህ ሊሳካ የሚችለው በእምነት በኩል እንደሆነ ጥቅሱ ያስረዳል፡፡ በክርስቶስ ላይ ያለን እምነት ነው የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆን የሚያደርገን፡፡

      ዮሐንስ 1፡12-13 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤››፡፡ ይህ ጥቅስ የእግዚአብሔር ልጅነት ስልጣን የተሰጣቸው እነማን እንደሆኑና ከእግዚአብሔር መወለድ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ይነግረናል፡፡ የልጅነት ስልጣኑ የተሰጠው ክርስቶስን ለተቀበሉ ሲሆን ይህን የሚያደርጉ አማኞች ከእንግዲህ ወዲያ ፍጥረታዊ ሰዎች ብቻ እንዳልሆኑ ጥቅሱ ያበስራቸዋል፡፡

      የእግዚአብሔር ልጅና ቤተሰብ ለመሆን ዳግም መወለድ ይኖርብናል፡፡ ጌታችን በዮሐንስ 3፡3 ላይ እንዲህ ያለ ማስጠንቀቂያ ያስተላልፍልናል፡- ‹‹ኢየሱስም መልሶ:- እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው››፡፡ በመቀጠል በዮሐንስ 3፡5 ላይ እንዴት ይህ ዳግም ልደት እንደሚከናወን ያስረዳናል፡- ‹‹ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል:- እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም››፡፡

      መንግስተ ሰማይን የሚወርሱት የእግዚአብሐር ልጆች ብቻ ናቸው፡፡ በ1ጴጥሮስ 1፡4 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል››፡፡ በክርስቶስ በማመን የእግዚአብሔር ልጅ ሆነዋል? ይህን ካላደረጉ በእግዚአብሔር ቃል መሰረት በሰማይ ርስት የሎትም፡፡

      ወድ አንባቢዬ የዘላለም ህይወት እንዳለን እርግጠኛ ነን በሚል ሃሳብ በተከታታይ ከክፍል 1 ጀምሮ እስከዚህኛው ክፍል ድረስ አብራችሁ ስላላችሁ አመሰግናለሁ ቀጣዩን ክፍልም አብረን እንቀጥላለን እስከዚያው ቸር እንሰንብት

      ካሱ ቦስተን

      የዘላለም ህይወት እንዳለን እርግጠኛ ነን ?

      ክፍል 5

      ክርስቶስ ቅጣታችንን ተቀብሎልናል !

      ሁላችን ኃጢአትን አድርገናል፡፡ እግዚአብሔር ጻድቅ ፈራጅ ስለሆነ ለኃጢአታችን የሚገባንን ፍርድ ልንቀበል ይገባናል፡፡ ይህም ደሞዝ ሞት ነው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ፍቅር ስለሆነ ልጁ ኢያሱስ ክርስቶስ ይህንን ቅጣት በእኛ ፈንታ ተቀብሎልናል፡፡ ሮሜ 5፡6-10 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና››፡፡ ይህን ፍቅር ለመረዳት አዳጋች ነው፡፡

      በተጨማሪ 1ጴጥሮስ 3፡18 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ክርስቶስ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንዲያቀርበን እርሱ ጻድቅ ሆኖ ስለ ዓመፀኞች አንድ ጊዜ በኃጢአት ምክንያት ሞቶአልና፤ በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ››፡፡ ዳግመኛ ወደ እግዚአብሔር እቅፍ እንድንመለስ ጻድቅ የሆነው ክርስቶስ ኃጥኣን በሆነው በእኛ ፈንታ መሰቃየት ነበረበት፡፡ ‹‹እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው›› (2ቆሮንቶስ 5፡21)፡፡ ክርስቶስ እኛ ፈጽሞ ልንሰራው የማንችለውን ሥራ ሰርቶልናል፡፡ እዳችንን ከፍሎልናል፡፡ የሰው ልጅ ይህንን እዳ መክፈል ቢችል ኖሮ ክርስቶስ በመስቀል ላይ መሞት ባላስፈለገው ነበር፡፡ በበደላችን ሙታን ነበርን፣ ነገር ግን ከወደደን ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ክርስቶስ በእኛ ፈንታ እንዲሞት በማድረግ የጽድቅ ፍርዱ ሳይዛባ ከሞት አዳነን፡፡

      ሰው የሚድንበት ብቸኛ መንገድ ክርስቶስ ብቻ ነው፡፡ ሌላ ምንም አማራጭ የለንም፡፡ ዮሐንስ 14፡6 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ኢየሱስም፡- እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም››፡፡ ወደ እግዚአብሔር የምንደርስበት መንገድ ክርስቶስ ነው፡፡ በተጨማሪ የሐዋሪያት ሥራ 4፡12 እንዲህ ይላል፡- ‹‹መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና››፡፡ በሙሐመድ፣ በቡድሃ፣ በአይሁድንት፣ ወይም በሌሎች በማናቸውም የሃይማኖት ስሞች መዳን የለም፡፡ እኛ በፈጠርነው የክርስትና ሃይማኖት ስርአቶችም ጭምር መዳን የለም፡፡ ድነታችን የምናገኘው እዳችንን በከፈለው በክርስቶስ ብቻ ነው፡፡

      እዳችንን ለመክፈል ክርስቶስ ተሰቃይቷል፡፡ የተቀበለውን መከራ ማሰብ አእምሮችን ፈጽሞ አይችልም፡፡ ክርስቶስ ወደዚህ አለም የመጣው በሞቱ እዳችንን ለመክፈል ነው፡፡ የክርስቶስን ሞት የሚተነብዩ በርካታ የብሉይ ኪዳን ጥቅሶች አሉ፡፡ ለአብነት ያህል ክርስቶስ ከመሞቱ ከ700 አመት በፊት የተነገረው የኢሳይያስ ትንቢት አንዱ ነው፡- ‹‹እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ›› (ኢሳይያስ 53፡5-6)፡፡ የክርስቶስ ሞት ድንገተኛ አይደለም፣ የሰውን ልጅ ለመቤዠት የእግዚአብሔር ዘላለማዊ እቅድ እንጂ፡፡

      ክርስቶስ ሁሉን በማወቅ ችሎታው ሊሆንበት ያለውን ሁሉ ያውቅ ነበር፡፡ በማቴዎስ 20፡17-19 እንዲህ የሚል ቃል እናነባለን፡- ‹‹ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ሊወጣ ሳለ፥ በመንገድ አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ብቻቸውን ወደ እርሱ አቅርቦ። እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፣ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች ይሰጣል፤ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል፥ ሊዘባበቱበትም ሊገርፉትም ሊሰቅሉትም ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል አላቸው››፡፡ ክርስቶስ ያለማንም አስገዳጅነት በፈቃዱ በእኛ ፈንታ ሊሞትልን ወሰነ፡፡

      ክርስቶስ በተዋህዶ ሰውም አምላክም ነው፡፡ ሊሆንበት ያለውን ከማወቅ ባሻገር ሥጋ እንደመልበሱ በሞቱ ተጨንቆ ነበር፡፡ ኢየሱስ ከሞቱ ቀን ቀደም ብሎ ባለው ምሽት በጌቴ ሰማኒ የአታክልት ሥፍራ በነበረበት ወቅት የነበረውን ሁኔታ በሉቃስ 22፡41-44 እንዲህ እናነባለን፡- ‹‹ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም። አባት ሆይ፥ ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር። ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው። በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ››፡፡ ክርስቶስ በእርግጥም በመስቀሉ ምጥ ነው ያዳነን፡፡

      በተጨማሪ በ1ጴጥሮስ 2፡24 ላይ የሚከተለውን እናነባለን፡- ‹‹ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ››፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ሆነን አንድንታይ ክርስቶስ የኃጢአታችንን እዳ መክፈል ነበረበት፡፡ ሰው በዚህ መንገድ ጻድቅ ሆኖ በእግዚአብሔር ዘንድ ሲታይ እግዚአብሔር ያዘጋጀውን የድነት ስጦታ ተቀብሏልና ከዘላለም ፍርድ ይድናል፡፡

      የመስቀል ሞት የሰው ልጅ ሰውን አሰቃይቶ ለመግደል ካበጃቸው የስቃይ ፍርዶች አሰቃቂው ነው፡፡ ከዚህ የባሰ የለም፡፡ ጌታችን በዚህ መስቀል ላይ መግለጽ በሚያስቸግር ስቃይና ጣር ለስድስት ሰአታት ቆየ፡፡ እግዚአብሔር እኛን በማዳን ስራ ውስጥ ጻድቅ ይሆን ዘንድ ቅጣታችንን በመቀበል ስለእኛ ሞተ፡፡ ምን አይነት ፍቅር ነው! እርሶና እኔ ቃሉን ለመታዘዝ ክርስቶስ የከፈለው ዋጋ በቂ ምክኒያታችን አይሆንምን? ስለዚህ የሃጢያታችንን ዋጋ ተቀብሎ የሞተልንን ጌታ አሁን በልባችን አምነን ብንቀበል የዘላለምን ህይወት እናገኛለን። ሌላ ደግሞ ከዚህ ቀጥሎ የእግዚአብሄር ልጅ የመባልን ስልጣን ያገኘንበትም ስለሆነ በቀጣዩ ክፍል እንገናኝ። ቸር እንሰንብት።

      ካሱ ቦስተን